23Jun2025 Read more በወንጀል ነክ ድርጊት ዉስጥ ገብተዉ ከተገኙ ህጻናት እንዲሁም በሴቶች እና ህጻናት ችሎት ለሚሰሩ የፌዴራል ዳኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት በወንጀል ነክ ድርጊት ዉስጥ ገብተዉ ከተገኙ ህጻናት እንዲሁም በሴቶች እና ህጻናት ችሎት ለሚሰሩ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዳኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰኔ 14 እና 15 ቀን 2017 ዓ.ም ተሰጥቷል፡፡
9Dec2024 Read more በተባበሩት መንግስታት የህጻናት መብቶች ኮሚቴ አማካኝነት እየተዘጋጀ ባለው General Comment 27 on Access to Justice for children ላይ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የግብዓት ማሰባሰቢያ ውይይት ተካሄደ በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናትና ፍትህ ፕሮጀክት በተባበሩት መንግስታት የህጻናት መብቶች ኮሚቴ አማካኝነት እየተዘጋጀ ባለው General Comment 27 on Access to Justice for children የሃገራችን ህጻናት አስተያየት ለማካተት በማሰብ ህዳር 28 ቀን 2017 ዓ.ም ከአዲስ አበባ የተለያዩ ትምህርት ቤቶች እና የህጻናት ፓርላማ የተውጣጡ ህጻናትን በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በማሰባሰብ ግብዓት ተቀብሏል፡፡
19Aug2024 Read more ፍርድ ቤቱ የህጻናት ቀለብ አወሳሰን መምሪያና የዳኞች ለህጻናት ተስማሚ ፍትህ የስልጠና ማንዋልን አስመረቀ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከዩኒሴፍ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር የህጻናት ቀለብ አወሳሰን መምሪያና የዳኞች ለህፃናት ተስማሚ ፍትህ የስልጠና ማንዋልን ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም አስመርቋል፡፡
18Jul2024 Read more የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአፍሪካ ህብረት በህጻናት ጥበቃ ጉዳዮች እና ሌሎች ጎጂ ተግባራት በኢትዮጵያ ሀገራዊ የክትትል ተልዕኮ ወርክሾፕ ላይ በመገኘት ሪፖርት አቀረበ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት "African Union Country Monitoring Mission/Workshop on Child Protection issues and other Harmful Practices in Ethiopia"በሚል የተዘጋጀ 3 ቀን ወርክሾፕ ላይ በመገኘት ፍርድ ቤቶች በህጻናት መብት እና ደህንነት ዙሪያ ያከናወኗቸው ስራዎች ላይ ገለጻ አድርጓል፡፡
26Jun2024 Read more በህጻናት ዝቅተኛ የወንጀል ተጠያቂነት እድሜ ላይ ያተኮረ ስልጠና እና ውይይት ከኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ጋር ተካሄደ በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ዳይሬክቶሬት እና በUNFPA ትብብር የህጻናት የወንጀል ተጠያቂነት ዝቅተኛ እድሜን በተመለከተ ሰኔ 15 ቀን 2016 ዓ.ም ከክቡራን የኢፌዴሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላት ጋር ውይይት ተደርጓል