25Mar2024 Read more በረቂቅ የህፃናት ፍትህ የስልጠና ሞጁል ላይ የግብአት ማሰባሰቢያ ዉይይት ተደረገ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ህፃናት ፍትህ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ከዩኒሴፍ (UNICEF) ጋር በመተባበር ያዘጋጀዉን የህፃናት ፍትህ የስልጠና ሞጁል ላይ የግብዓት ማሰባሰቢያ ዉይይት መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም አድርጓል፡፡
14Dec2023 Read more ወንጀል ነክ ነገር ዉስጥ ገብተዉ የተገኙ ወጣቶችና በሴቶችና ህጻናት ችሎት ያጋጠሙ መልካም ተሞክሮዎችና ተግዳሮቶች (Children in conflict with the law) በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ከፌደራልና ክልል ፍርድ ቤቶች ከተዉጣጡ ዳኞችና ማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች ጋር የምክክር መድረክ ተካሄደ፡፡ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ከዓለም አቀፉ የህጻናት አድን ድርጅት (Save The Children) ጋር በመተባበር ወንጀል ነክ ነገር ዉስጥ ገብተዉ የተገኙ ወጣቶችና በሴቶችና ህጻናት ችሎት ያጋጠሙ መልካም ተለሞክሮዎችና ተግዳሮቶች (Children in conflict with the law) በሚል ርዕስ በተዘጋጀው የምክክር መድረክ 50 የሚጠጉ ከፌደራልና ክልል ፍርድ ቤቶች የተዉጣጡ ዳኞችና ማህበራዊ ሳይንስ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል፡፡
9Aug2023 Read more የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ለፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የህጻናት ማቆያ የሚሆኑ ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ህጻናት ፍትህ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አዲስ ለሚያሰራው የህጻናት ማቆያ የሚሆን ግምታቸው ብር 35,000 (ሰላሳ አምስት ሺህ) ብር የሚያወጡ የተለያዩ ቁሳቁሶች ድጋፍ አደረገ፡፡
30Jun2023 Read more በቤተሰብ አስማሚነት ላይ የተዘጋጀ የሥልጠና እና የውይይት መድረክ ተካሔደ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በፍርድ ቤት መር አስማሚነት በተለይም በቤተሰብ አስማሚነት (Family mediation) ላይ ለፌደራል ፍርድ ቤት ረዳት ዳኞች እና ለሶሻል ወርክ ባለሙያዎች ያዘጋጀው የሥልጠና እና የውይይት መድረክ በኢንተር ኮንቲኔታል ሌግዢሪ ሆቴል ተካሄዷል፡፡
19Jun2023 Read more ተወላጅነትን በማረጋገጥ እና በመካድ ክርክር እንዲሁም በዘረመል ምርመራ አጠቃቀም ላይ የተዘጋጀ የሥልጠና እና የውይይት መድረክ ተካሔደ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሕጻናት ፍትሕ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ተወላጅነትን በማረጋገጥ እና በመካድ ክርክር እንዲሁም በዘረመል ምርመራ አጠቃቀም ላይ ለፌደራል ፍርድ ቤት ዳኞች ያዘጋጀው የሥልጠና እና የውይይት መድረክ ከሰኔ 10-11 ቀን 2015 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ተካሒዷል፡፡