23Jan2026 Read more በ19ኛው የአፍሪካ ሕገ መንግሥታዊ ፍ/ቤቶችና መሰል ተቋማት የሥራ አስፈፃሚዎች ስብሰባ ላይ የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በአልጀሪያ አልጀርስ ከተማ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደረገለት። የፌዴራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት እና የኢፌዴሪ የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ ሰብሳቢ በሆኑት ክቡር አቶ ቴዎድሮስ ምህረት እና በአጣሪ ጉባዔ ጽ/ቤቱ ዋና ዳይሬክተር በአቶ ደሳለኝ ወዬሳ የተመራው የኢትዮጵያ ልዑክ ማክሰኞ ጥር 12 ቀን 2018 ዓ.ም አልጀርስ ሲደርስ በአልጀሪያ ሕገ መንግሥታዊ ፍ/ቤት ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል።
22Jan2026 Read more የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኢኮርት ትግበራ ላይ ለፍትህ ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎች ገለጻ ተደረገ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት አገልግሎቱን በቴክኖሎጂ ለማዘመን እያከናወናቸው ካሉት ተግባራት መካከል የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት ዝርጋታ አንዱ ሲሆን ፍርድ ቤቱ ከኢትዮቴሎኮም ጋር በጋራ በመሆን የፌዴራል ፍርድ ቤቶችን በኔትወርክ የሚያስተሳስር የዋይድ ኤርያ ኔትወርክ ዝርጋታ መጠናቀቁን ተከትሎ በመሰረተ ልማቱ ላይ ተግባራዊ የሚደረጉ መተግበሪያዎችን አልምቷል፡፡
13Jan2026 Read more በአገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋዩች አያያዝ ላይ ስልጠና ተሰጠ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰው ሃብት ስራ አመራር ዳይሬክተሮች፣ ቡድን መሪዎች፣ በሬጅስትራር ስር ላሉ እና ለሌሎች የአስተዳደር ዘርፍ ሰራተኞች ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም በአገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋዩች አያያዝ ላይ ስልጠና ተሰጥቷል ፡፡
13Jan2026 Read more በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በወንጀል ችሎት በሚታዩ ችግሮችና መፍትሄዎች ዙሪያ በተደረገ ጥናት የግብዓት ማሰብሰቢያ ዉይይት ተደረገ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በፌዴራል ፍርድ ቤቶች በወንጀል ችሎቶች የሚታዩ ተግዳሮቶችና መፍትሔዎች ዙሪያ በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ላይ ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም የግብዓት ማሰባሰቢያ ዉይይት ተካሄዷል፡፡
13Jan2026 Read more የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት እጩ ዳኞችን ሹመት አጸደቀ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ታህሳስ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደዉ 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ስብሰባ በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 81(2) መሰረት 34 የከፍተኛ ፍርድ ቤት እጩ ዳኞችን ሹመት አጽድቋል፡፡