Fee Calculator

የፌደራል ፍርድ ቤቶች የዳኝነት ክፍያን ለመወሰን የወጣ ደንብ ቁጥር 1/2017 መሰረት የተሰራ

በገንዘብ ሊተመኑ የሚችሉ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን ክስ ለማቅረብ ስለሚከፈል የዳኝነት ክፍያ መጠን ከታች የገንዘቡን መጠን በማስገባት ያስሉ።

የቀጥታ ክስ ዳኝነት ክፍያ:


{{formattedFee}}

የይግባኝ ዳኝነት ክፍያ:


{{judgeAppealPayment}}

የሰበር ዳኝነት ክፍያ:


{{judgeCassationPayment}}

ሌሎች በደንብ 1/2017 የተካተቱ

  1. አቤቱታው የቀረበው ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሆነ ብር 1,000 (አንድ ሺህ ብር) ይከፈላል።
  2. አቤቱታው የቀረበው ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሆነ ብር 1,500 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር) ይከፈላል።
  3. አቤቱታው የቀረበው ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሆነ 2,000 (ሁለት ሺህ ብር) ይከፈላል።
  4. በቤተሰብ ሕግ መሰረት በባልና ሚስት መካከል ንብረትን አስመልክቶ የሚደረግን ውል በፍርድ ቤት ለማረጋገጥ የሚቀርብ አቤቱታ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ይከፈላል።
  5. ጊዜው ያለፈበት የይግባኝ ወይም የሰበር ማስፈቀጃ አቤቱታ ለማቅረብ ብር 100 (አንድ መቶ ብር) ይከፈላል፡፡
  6. በግልግል ዳኝነት ዳኝነት ጉባኤ በሚታይ ጉዳይ ጊዜያዊ የመጠባበቂያ እርምጃ ወይም የእግድ ትዕዛዝ እንዲሰጥ ወይም ሌላ ትዕዛዝ ተፈፃሚ እንዲሆን ለሚቀርብ ማናቸውም አቤቱታ ብር 2,000 (ሁለት ሺህ ብር) ይከፈላል፡፡

በአቤቱታ አቅራቢው ከአንድ በላይ የክስ ምክንያቶችን በአንድ ላይ አጣምሮ በሚያቀርብበት ጊዜ ለእያንዳንዱ የክስ ምክንያት አግባብነት ባለው የዚህ ደንብ ድንጋጌ መሰረት ተሰልቶ የዳኝነት ክፍያ ይከፈላል፡፡

  1. በዚህ ደንብ ወይመ በሌላ ሕግ ከዳኝነት ክፍያ ነጻ ከተደረጉ ወጎኖች በስተቀር በፍርድ ቤት ለሚሰጡ ማናቸውም አገልግሎቶች ክፍያ መፈጸም አለበት።
  2. ከዚህ በታች ለተመለከቱት አገልግሎቶች የሚከፈለው ክፍያ እንደሚከተለው ይሆናል:-
    • ሀ. ለተከራካሪ ወገን ወይም ለምስክር መጥሪያ ለማውጣት ለእያንዳንዱ ምስክር ብር 50 (ሃምሳ ብር) ይከፈላል፡፡።
    • ለ. የፍርድ ወይም በመዝገብ ውስጥ የሚገኝ ማናቸውም የሰነድ ወይም የኤሌክትሮኒክስ ሰነድ በፍርድ ቤቱ ኮፒ ተደርጐ የሚሰጠው ከሆነ በገፅ ብር 5 (አምስት ብር) ይከፈላል።
    • ሐ. ከላይ ከተመለከቱት አገልግሎቶች ውጪ ከፍርድ ቤቱ ከተጠየቀ ፍርድ ቤቱ ከዚህ በላይ ከተመለከቱት ጋር ተመሳሳይ በሆነ ርዕስ ሥር የተመከተው ክፍያ እንዲከፈል ያደርጋል።

በህግ በተሰጠ ሥልጣን መሰረት በተለያዩ የአስተዳደር ተቋማት ታይተው ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዳዮች በፍርድ ቤት በይግባኝ ወይም በቀጥታ ክስ ለሚቀርብ አቤቱታ ከዚህ በታች የተመለከተው ክፍያ ይከፈላል።

  1. አቤቱታው የቀረበው ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሆነ ብር 1,000 (አንድ ሺህ ብር) ይከፈላል።
  2. አቤቱታው በይግባኝ የቀረበው ለከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሆነ ብር 2000 (ሁለት ሺህ ብር) ይከፈላል።
  3. አቤቱታው የቀረበው ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሆነ 3000 (ሶስት ሺህ ብር) ይከፈላል።
  4. በአስተዳደር አካል የተሰጠው ውሳኔ እንዲከለስ አቤቱታ የቀረበው ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ከሆነ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ይከፈላል።
  5. በአስተዳደር አካል የተሰጠው ውሳኔ እንዲከለስ አቤቱታ የቀረበው ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከሆነ ብር 1000 (አንድ ሺህ ብር) ይከፈላል፡፡
  6. በአስተዳደር አካል የተሰጠው ውሳኔ እንዲከለስ አቤቱታ የቀረበው ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከሆነ ብር 1500 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር) ይከፈላል

አቤቱታ የቀረበለት ፍርድ ቤት በጉዳዩ ላይ ፍርድ፣ ውሳኔ ወይም ትዕዛዝ ከሰጠ በኋላ ወይም በክርክር ሂደት ጣልቃ ለመግባት በቀረበ አቤቱታ ለሚሰጥ አገልግሎት ቀጥሎ የተመለከተው የዳኝነት ክፍያ ይከፈላል፡-

  1. ተከሳሽ በሌለበት የተሰጠን ውሳኔ አስነስቶ ወደ ክርክሩ ለመግባት ለሚቀርብ አቤቱታ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) የዳኝነት ክፍያ ይከፍላል፡፡
  2. ፍርድን ለመቃወም ለሚቀርብ አቤቱታ መቃወሚያውን ያቀረበው ወገን አስቀድሞ ተከፍሎ በነበረው ክፍያ ልክ የዳኝነት ክፍያ ይከፈላል።
  3. በክርክር ሂደት ጣልቃ ለመግባት ለሚቀርብ አቤቱታ የክርክሩ የገንዘብ መጠን ከግምት ሳይገባ አመልካቹ ብር 1000 (ኣንድ ሺህ ብር) የዳኝነት ክፍያ ይከፍላል።

ከተከራካሪ ወገኖች አንዳቸው በክርክር ሂደት ውስጥ የአቤቱታ ማሻሻል ጥያቄን ጨምሮ በሚያቀርቡት ማመልከቻ ምክንያት ሂደቱ ወደኋላ የሚመለስ ከሆነ የደረሰበትን ደረጃ፣ የፍርድ ቤቱን ጊዜ እና ወጪ ከግምት ውስጥ በማስገባት አቤቱታ አቅራቢው መጀመሪያ በቀረበው ክስ ላይ ተከፍሎ የነበረውን የዳኝነት ክፍያ 10 ከመቶ (አስር ከመቶ) የማይበልጥ እንዲከፍል ችሎቱ ትእዛዝ ሊሰጥ ይችላል፡፡

ፍርድ ከተፈረደ በኋላ ፍርድ ለማስፈፀም ለሚቀርብ የአፈጻጸም ማመልከቻ ቀጥሎ በተመለከተው መሰረት የዳኝነት ክፍያ ይፈጸማል፡-

  • ሀ. ፍርድ ያረፈው ከዜሮ እስከ ብር 100,000 (ኣንድ መቶ ሺህ ብር) ከሆነ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) ይከፈላል፤
  • ለ. ፍርድ ያረፈው ከብር 100,001 (አንድ መቶ ሺህ አንድ ብር) እስከ ብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ከሆነ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ይከፈላል፤
  • ሐ. ፍርድ ያረፈው ከብር 200,001 (ሁለት መቶ ሺህ አንድ ብር) አስከ 500,000 (አምስት መቶ ሺህ ብር) ከሆነ ብር 1000 (አንድ ሺህ ብር) የዳኝነት ይከፈላል፤
  • መ. ፍርድ ያረፈው ከብር 500,001 (አምስት መቶ ሺህ አንድ ብር) አስከ 1,000,000 (አንድ ሚሊዮን ብር) ከሆነ ብር 1500 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር) የዳኝነት ይከፈላል፤
  • ሠ. ፍርድ ያረፈው ከብር 1,000,001 (አንድ ሚሊዮን አንድ ብር ) እስከ ብር 10,000,000 (አሥር ሚሊዮን ብር) ብር ከሆነ 2000 (ሁለት ሺህ ብር) የዳኝነት ይከፈላል፤
  • ረ. ፍርድ ያረፈው ከብር 10,000,001 (አሥር ሚሊዮን አንድ ብር) በላይ ከሆነ ብር 3000 (ሶስት ሺህ ብር) የዳኝነት ይከፈላል፤
  • ሰ. በፍርድ አፈጻጸም ወቅት የተያዘ ወይም የተከበረ ንብረት ላይ መብት አለኝ የሚል ሰው አቤቱታ ሲቀርብ አቤቱታ አቅራቢው ፍርዱ ሊፈጸምብኝ አይገባም የሚለው ንብረት ወይንም ገንዘብ መጠን ከግምት ሳይገባ ብር 1000 (አንድ ሺህ ብር) የዳኝነት ክፍያ ይከፍላል
  • ሸ. የፍርድ አፈጻጸሙ በገንዘብ ሊተመን የማይችል ጉዳይን የተመለከተ ከሆነ ብር 500 (አምስት መቶ ብር) ይከፈላል፡፡

የዳኝነት ክፍያ: {{ result }}

ለዳኝነት የተከፈለ ገንዘብ ከዚህ በተመለከተው አግባብ ለክፋዩ ሊመለስ ይችላል

  1. ከሳሽ የሆነው ወገን የዳኝነት ክፍያውን ፈጽሞ መዝገቡ ተጠሮ ከመያዙ በፊት ወይም ቀጠሮ እንደተሰጠው መጥሪያው ወጪ ከመሆኑ በፊት ክሱን ለማቋረጥ ቢወስን ለዳኝነት ከከፈለው ገንዘብ ላይ 5 በመቶ (አምስት በመቶ) ተቀንሶ ቀሪው ይመለስለታል
  2. ክስ የቀረበለት ፍርድ ቤት መዝገቡን መርምሮ ከሳሹ ክስ ለማቅረብ የሚያስችል መነሻ ምክንያት የለውም ወይም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት ሥልጣን የለውም በማለት መዝገቡን ቢዘጋ ከተከፈለው ዳኝነት ላይ 10 በመቶ (አሥር በመቶ) ተቀንሶ ቀሪው ለከሳሹ ይመለስለታል፡፡
  3. ከክስ መሰማት በፊት ከስ ቢቋረጥ ከተከፈለው ዳኝነት 15በመቶ (አሥራ አምስት በመቶ) ተቀንሶ ቀሪው ተመላሽ ይደረጋል፡፡
  4. ዳኝነት ተከፍሎ የተከፈተ መዝገብ ጉዳዩ በዳኛ አማካኝነት ለፍርድ ቤት መር አስማሚ ተመርቶ ጉዳዩ በአስማሚ በኩል እልባት ካገኘ ከሳሹ ወይም ይግባኝ ባዩ ለዳኝነት የከፈለው ገንዘብ በፍርድ ቤት መር አስማሚነት መመሪያ ላይ በተቀመጠው አግባብ ተመላሽ ይደረጋል፡፡
  5. ተከራካሪ ወገኖች ክርክራቸውን ከክስ መስማት በፊት በስምምነት ወይም በእርቅ ቢጨርሱ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ 2 ላይ በተመለከተው መሰረት ከተከፈለው ዳኝነት ላይ ተቀንሶ ለከሳሸ ይመለሳል፡፡ ተከሳሹም የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ አቅርቦ ከሆነ በዚሁ አግባብ ይፈጻማል፡፡
  6. ከሳሹ ከክስ መስማት በኋላ ክሱን ቢያነሳ የዳኝነት ክፍያው ሙሉ በሙሉ አይመለስም፡፡

በሌሎች ሕጎች የተደነገጉት እንደተጠበቀ ሆኖ ከዚህ በታች በተጠቀሱት ጉዳዮች ላይ የዳኝነት ክፍያ አይከፈልም

  1. የተለብ ክፍያና የልጅ አስተዳደግን አስመልክቶ የሚቀርብ አቤቱታ
  2. በሴቶች፣ በሕጻናት፣ በእረጋዊያን፣ ኣካል ጉዳተኞችን እንዲሁም ሌሎች ለመብት ጥሰት ተጋላጭ የሆኑ የኀብረተሰብ ክፍሎችን በተመለከተ የሚቀርብ የሕዝብ ጥቅምን ለማስክበር ወይም አካልን ነጻ ለማውጣት እና ሌሎች የወል ሰብዓዊ መብታቸዉን ለማስክበር በሲቪል ማኅበራት አማካይነት የሚቀርብ ክስ፤
  3. የአካባቢ ጥበቃና እንክብካቤን በሚመለከት የሚቀርቡ ጉዳዮችን፤
  4. በሕግ አግባብ በድሃ ደንብ እንዲከራከር በፍርድ ቤት የተወሰነለት ሰው
  5. በወንጀል ጉዳይ የሚቀርብ ክርክር
  6. አግባብነት ባለዉ ሕግ መሰረት አንድ ሰራተኛ በግሉ በአስተዳደር አካል የተሰጠው ውሳኔ በፍርድ ቤት እንዲከለስለት ለሚያቀርበዉ እቤቱታ