መ/ር ሲራጅ መሀመድ እና የኢትዮጵያ መድን ድርጅት ሰ/መ/ቁ፡-200948
ጉዳዩ ከውል ውጭ ኃላፊነትን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነዉ፡፡የአሁኑ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን የአሁኑን አመልካች ጨምሮ ሌሎች 4 ሰዎች ላይ ባቀረበው ክስ ንብረትነቱ ከተከሳሾች የአንዳቸው ወይም የሁሉም የሆነ የሠ/ቁ.1-06754 አ.አ የሆነ ተሽከርካሪ በ25/04/2006ዓ.ም በኮልፈ ቀራንዮ ክ/ከተማ ወረዳ 4 አለም ባንክ አከባቢ ተጠሪ የመድን ሽፋን የሰጠውን የሰ/ቁ.4-01850ኢ.ት የሆነውን ተሽከርካሪ በመግጨት ጉዳት አድርሷል፡፡ተጠሪ ከደንበኛው ጋር ባለው ውል ስምምነት ለደረሰው ጉዳት ብር 19,250.00 ለደንበኛው ከፍሏል፣ስለሆነም ተከሳሾች ገንዘቡን እንዲተኩ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡አመልካች በበኩሉ አደጋ አድራሹን ተሽከርካሪ በ2005 ዓ.ም ለአቶ ጉግሳ ይልማ በመሸጥ መኪናውን ያስረከብኩት ስለሆነ ደረሰ ስለተባለው ጉዳትም የማውቀው ነገር የለም፣በእኔ ላይ የቀረበው ክስ አለአግባብ ነው በማለት መልስ ሰጥቷል፡፡ሌሎች ተከሳሾች መልስ አላቀረቡም ቀርበውም አልተከራከሩም ተብሎ የታለፈ መሆኑን መዝገቡ ያሣያል፡፡…………………..
12645
Documents to download
-
200948(.pdf, 768.11 KB) - 1135 download(s)