አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም እና አቶ ነጋሽ ያደቴ አባይነህ ነጋሽ ሰ.መ.ቁ.200968
ይህ የእርሻ መሬት የተጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን፣ የአሁን አመልካች የሥር ከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር። ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ.ቁ.251106 ጥቅምት 26 ቀን 2013 ዓ.ም የሰጠዉ ትዕዛዝ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ።የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ ከሳሽ በሥር ፍ/ቤት ባቀረበዉ ክስ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል ዉስጥ ግብር እየገበርኩበት ያለዉን ሁለት ቀርጥ (አዋሳኝ በመጥቀስ) የእርሻ መሬት ይዞታዬን የካቲት ወር 1989 ዓ.ም ባደረግነዉ ዉል ለጊዜያዊ ችግሬ መዋያ ብር 7000 (ሰባት ሺህ) ከተከሳሽ ተቀብዬ መሬቱን ለተከሳሽ የሰጠሁ፣ ገንዘቡን ስመልስለት ደግሞ መሬቱን ሊመልስልኝ የተስማመን ሲሆን፣ ተከሳሽ ገንዘቡን ተቀብሎኝ መሬቱን እንዲያስረክበኝ ፈቃደኛ ስላልሆነ፣ ተከሳሽ ገንዘቡን ተቀብሎኝ የእርሻ መሬቱን እንዲያስረክበኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡……………..
12162
Documents to download
-
200968(.pdf, 737.05 KB) - 1185 download(s)