አቶ ረጋሳ ጉርሙ እና ወ/ሮ ዘነበች ገ/መንፈስ ሰ/መ/ቁ፡-202737
የሰበር አቤቱታ የቀረበዉ ያለፍርድ ቤት ፈቃድ በተወዉ ጉዳይ ላይ የቀረበዉ ክስ ተቀባይነት የለዉም ተብሎ የተሰጠዉን ብይን ለማስለወጥ ነዉ፡፡የክርክሩ መነሻ የቤት ሽያጭ ውል የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ላይ የአሁኑ አመልካች ከሳሽ በመሆን የአሁኑ ተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ተጠሪ ከሟች ባለቤታቸው አቶ ተሾመ አፈወርቅ ጋር በመሆን በቀን 06/12/1996 ዓ.ም በአ/አ/ከ/ቂ/ክ/ከተማ ወረዳ 02 የቤት ቁጥር 047 የካርታ ቁጥር ሴ.ኬ.አሲ/02/31/1229/001040/01 የሚታወቅ መኖሪያ ቤት ለአመልካችና ለአቶ ፀጋዬ ገ/መንፈስ ሽጠዋል፣ቤቱን እንዲለቁ ሲጠየቁ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ/ቁ/153563 ቤትን አንዲለቁልኝ ክስ አቅርቤ ፍ/ቤቱን አስፈቅጄ ያነሳሁት ቢሆንም ተጠሪ ቤቱን ለመልቀቅ ፈቃደኛ ስላልሆኑ ተጠሪ ቤቱን ለቀው እንዲወጡና እንዲያስረክቡኝ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋዋል፡፡……………
11957
Documents to download
-
202737(.pdf, 1.03 MB) - 1400 download(s)