እና አቶ ሰይድ እንድሪስ እና እና የሸዋ ሮቢት ከተማ አስተዳደር አገልግሎት ጽ/ቤት የሰ/መ/ቁ፡-205889
ጉዳዩ የውርስ ሀብት ነዉ የተባለዉን የመሬት ይዞታ አስለቅቆ ለመረከብ በቀረበ ክስ መነሻ የተሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል ተብሎ የቀረበ አቤቱታ የሚመለከት ነዉ፡፡ አመልካቾች በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ ሮቢት ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በተጠሪዎች ላይ በመሰረቱት ክስ ሟች አባታችን እንድሪስ አደም ከባለቤቱ ከስር 1ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ አሊያ አህመድ ጋር በባልና ሚስት በነበሩበት ጊዜ ከ1966 ዓ/ም ጀምሮ ይዘዉ በኋላም በ1989 ዓ/ም በነበረው የመሬት ሽግሽግ በሕጋዊ መንገድ ተደልድሎ የተሰጣቸዉ እና ከ1978 ዓ/ም ጀምሮ ግብር የሚገብሩበት በሸዋ ሮቢት ከተማ 05 ቀበሌ ውስጥ አዋሳኞቻቸዉ በክሱ የተጠቀሰ ልዩ ቦታዉ እስላም ቀብር ተብሎ በሚታወቅበት አካባቢ 2 ጥማድ መሬት፣ልዩ ቦታዉ ንብ እርባታ ተብሎ በሚታወቅበት አካበቢ 1 ጥማድ መሬት እንዲሁም እንስርቱ ዉሃ ተብሎ በሚጠራበት አካባቢ እሩብ ጥማድ መሬት 1ኛ ተከሳሽ ለብቻቸዉ ይዘዉ እየተጠቀሙ ሊያካፍሉን ፈቃደኛ ስላልሆኑ ድርሻችንን እንዲያካፍሉን ይወሰንልን፡፡ እንዲሁም 2ኛ ተጠሪ አለአግባብ ስለያዘብኝ ለቆ እንዲያስረክበን ይወሰንልን በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡እንደሚከተለው ቀርቧል…………….
7611
Documents to download
-
205889(.pdf, 1.03 MB) - 738 download(s)