ኮ/ል ተክለብርሃን ገ/መድህን እና የደ/ዕዝ ወታደራዊ ዓ/ህግ የሰ/መ/ቁ፡- 204813እና206556
ክርክሩ የተጀመረው የአሁን ተጠሪ መስከረም 4 ቀን 2013 ዓ.ም በአመልካቾች ላይ በኢፌዲሪ የቀዳሚ ወታደራዊ ፍ/ቤት ባቀረበው የመጀመሪያ ክስ አመልካቾች የመከላከያ ሰራዊት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1100/2011 አንቀጽ 2 (12)፣ የኮቪድ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር በወጣው አስቸኳይ አዋጅ ቁጥር 3/2012 በወንጀል ህግ አንቀጽ 32/1/ሀ እና 298/2/ የተደነገገውን በመተላለፍ ሰኔ 23 ቀን 2012 በግምት ከምሽቱ 3፡30 ሲሆን የተደራጁ ህገወጥ ቡድኖች ገጀራ ፣ፌሮ ብረትና ዱላ በመያዝ በሻሸመኔ ከተማ የህብረተሰቡን ንብረት እያቃጠሉ እያወደሙና እየዘረፉ በመሆኑ በክፍሉ አመራር ሜ/ር ጀኔራል ሹማ አብዴታ በስልክ ይህንን ህገወጥ ተግባር ተመጣጣኝ እርምጃ በመውሰድ እንዲቆጣጠሩ እና ህብረተሰቡን እንዲታደጉ የሰጣቸውን ትዕዛዝ በመጣስ ትዕዛዙን ሳይፈጽሙ ቀርተዋል በማለት የከሰሰ ሲሆን፤በሁለተኛው ክስም አመልካቾች የመከላከያ ሰራዊት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1100/2011 አንቀት 2/12፣ የኮቪድ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር በወጣው አስቸኳይ አዋጅ ቂጥር 3/2012 እና በኢፌዲሪ ወንጀል ህግ ቁጥር 32/1/ሀ እና 293/2/ የተደነገገውን በመተላለፍ፣ በ1999 ዓ.ም የወጣውን የመከላከያ ሰራዊት ቋሚ የግዳጅ አፈጻጸም ደንብ ቁጥር መከ-002/1999 ተ.ቁ 6.3 እና 7.5 መሰረት ሰራዊቱ ማናቸውም ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ሲደርሱ አደጋውን ለማስቆም ተመጣጣኝ እርምጅ በመውሰድ ህዝቡን ከአደጋ መታደግ እንዳለበት በግልጽ ተደንግጎ እያለ በተደራጁ ህገወጥ ቡድኖች የህብረተሰቡ ህይወት አደጋ ላይ ሲወድቅ ንብረት በከፍተኛ ሁኔታ ሲዘረፍ ሲቃጠል የስር አመልካቾች ግዳጅ ላይ እያሉ በመከላከያ ሀይሎች የአገልግሎት ደንብ መሰረት ተመጣጣኝ እርምጃ በመውሰድ ህብረተሰቡን ከአደጋ ባለመታደጋቸው ጉዳት ሊደርስ ችሏል በማለት ክስ መስርቶባቸዋል፡፡……………….
13211