የየካ ክ/ከተማ ዐቃቤ ህግ ፅ/ቤት እና እነአቶ ብሩክ ወንድሙሰ/መ/ቁ፡-204866
ለዚህ የሰበር ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ ሊቀርብ የቻለው አመልካች መጋቢት 20 ቀን 2013 ዓ.ም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአመልካችን በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.358 የቀረበን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ የሰጠውን ውሳኔ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከውጤት አንፃር ማፅናቱ መሰረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈፀመበት በመሆኑ ይኸው እንዲታረምልኝ በማለት ያቀረበውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ ሲሆን አመልካች በስር ፍርድ ቤት የመ/አመልካች የነበረ ሲሆን ተጠሪዎች የመ/ተጠሪዎች ነበሩ፡፡አመልካች በስር ፍርድ ቤት በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.358 መሰረት ባቀረበው አቤቱታም አመልካች በአዋጅ ቁጥር 64/2011 መሰረት የአስተዳደሩን እና የነዋሪዎችን መብት እና ጥቅም በማስከበር በማናቸውም የዳኝነት አካል ዘንድ የመቃወም አቤቱታ የማቅረብ መብት እንዳለው በመግለፅ በመቃወም ተጠሪዎች እና በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ፅ/ቤት መካከል በተደረገው ክርክር ላይ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ውሳኔ መብቴን የሚነካ በመሆኑ ሊሰረዝ ይገባል በማለት አመልክቷል፡፡………………….
12910
Documents to download
-
204866(.pdf, 717.73 KB) - 1287 download(s)