Tuesday, June 7, 2022 / Categories: CASSATION, 2013, Cassation አቶ በዳሳ ገለታ እና የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የሰ/መ/ቁ. 204392 ጉዳዩ የጉዳት ካሳን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በምዕራብ ወለጋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አመልካች በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡት ክስ ተጠሪዎች በላሎ ወረዳ እናንጎ ከተማ ቀበሌ 01 ውስጥ ልዩ ስሙ ሰሜን ጊዮርጊስ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የሚገኘውን፣ የካርታ ቁጥሩ 0738 የሆነውን እና ግምቱም ብር 220,000.00 የሆነውን ቤቴን 1ኛ ተጠሪ ለ2ኛ ተጠሪ ከተማውን አቋርጦ የሚያልፈውን መንገድ እንዲሰራ በውል ሰጥቶት 2ኛ ተጠሪ መንገዱን በሚሰራበት ወቅት ከቤቴ ፊት ለፊት የቆለለው አፈር በ2009 ዓ.ም የክረምት ወቅት በዝናብ ተንዶ ያፈረሰብኝ በመሆኑ ተጠሪዎች አሁን ለደረሰብኝ እና ወደፊት ሊደርስብኝ የሚችለውን ጉዳት በማይነጣጠል ኃላፊነት ካሳ እንዲከፍሉኝ ይወሰንልኝ በማለት የጠየቀዉን ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ፡፡መልካም ንባብ ……… Print 7949