/ Categories: CASSATION, Judgement, Cassation

አቶ ደሣለኝ ሲሳይ እና ወ/ሮ ድማም ተክሉ የሰ/መ/ቁ፡-196963

የሰበር አቤቱታ የቀረበው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት የሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በሚል ነው፡፡ አመልካች በሥር ፍርድ ቤት ጣልቃ ገብ ሲሆኑ 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ እና 2ኛ ተጠሪ ተከሳሽ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በ2ኛ ተጠሪ ላይ በመሰረቱት ክስ ከባለቤቴ አቶ አዘነ በየነ ጋር የባንክና የዕቁብ ዕዳ ስለነበረብን በቡራዩ ከተማ ዉስጥ የነበረንን ቤት በቀን 24/08/1999 ዓ/ም በተደረገ ዉል ሽጠን በሱሉልታ ከተማ ቁምቡሬ በተባለ ቦታ በካርታ ቁጥር ሱል/243/2005 ሆኖ የሚታወቀዉን ቤት የአሁን 2ኛ ተጠሪ ልጃችን ስለሆነ በስሙ ከአቶ ዳዊት አለሙ ላይ ገዝተናል፡፡ ይሁን እንጂ ባለቤቴ በሞት ሲለይ አመልካች ቤቱን ስለያዘብኝ ቤቱንና ሰነዱን እንዲያስረክበኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡……………..

Previous Article ተክለብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን ኃላ/የተ/የግ ማኅበር እና የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሰ/መ/ቁ 196340
Next Article እነ ወ/ሮ መሠለች ደስታ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ዐቃቤ ሕግ ቢሮ የሰ/መ/ቁ.193168
Print
12883

Documents to download

  • 196963(.pdf, 749.65 KB) - 1028 download(s)