/ Categories: CASSATION, Judgement, 2013, Cassation

አቶ ደጋረገ ሙሉ እና ወ-ሮ ውብናት ላቀ የሰ-መ-ቁ 181649

ይህ የባልና ሚስት የንብረት ክፍፍል ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል በሜጫ ወረዳ ፍ/ቤት ሲሆን፣ የአሁን አመልካች የሥር ተጠሪ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር አመልካች ሆኖ ሲከራከሩ ነበር። ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ.74190 ግንቦት 13 ቀን 2011 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ። የአሁን ተጠሪ በሥር በወረዳዉ ፍ/ቤት ባቀረበችዉ ክስ ከአሁን አመልካች ጋር ያለን ጋብቻ እንዲፈርስ፣ በጋራ የፈረናቸዉ ንብረቶች እንዲንካፈል በማለት ዘርዝራ በማቅረብ እንዲወሰንላት ዳኝነት ጠይቃለች።የአሁን አመልካች በዚህ ክስ ባቀረቡት መልስ ተጠሪዋ ባቀረበችዉ የንብረት ጥያቄ ላይ ተገቢ ነዉ ያለዉን ክርክር ያቀረበ ሲሆን፤ በራሱ በኩል ባቀረበዉ የተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ከተጠሪ ጋር ሊንካፈል ይገባል የሚላቸዉን ንብረቶች በመዘርዘር በመጠየቅ፤ የሰራተኛ እዳ አራት ኩንታል በቆሎ አንድ ኩንታል ዳጉሳ፣ አንድ ኩንታል ጓያ አለብን ልንከፍል ይገባል በማለት ጠይቋል። የአሁን ተጠሪ በዚህ በተከሳሽ ከሳሽነት ክስ ላይ መልስ ያቀረበች ሲሆን፣ የሰራተኛ የጋራ እዳ አለብን በማለት የቀረበዉም ሐሰት ነዉ፣ ይህ ተቀጠረ የተባለዉ ልጅ የአሁን አመልካች የግል ልጅ ነዉ የእኔም ሶስት ልጆች የግል ነበረኝ የግል ከብቶች ነበራቸዉ እነዚህ ልጆች አብራዉ ከእኛ ጋር ያደጉ ሲሆን ለሰሩበት ልንከፍላቸዉ አልተስማማንም አልቀጠርናቸዉም፣የአሁን አመልካች ልጅ እንደልጅ ከቤት ነበረ እንጂ የተቀጠረ አይደለም።ከዚህ በኋላ የወረዳዉ ፍ/ቤት የሰዉ ምስክሮች በመስማት በሰጠዉ ዉሳኔ የአሁን አመልካች በተከሳሽ ከሳሽነት የጋራ ዕዳ በማለት ያቀረበዉ የሰራተኛ እዳ 6 [ስድስት] ማዳበሪያ እህል በጋራ ሊከፍሉ ይገባል፤ የባልና ሚስት ንብረቶች ላይ ተገቢ ነዉ ያለዉን ዉሳኔ ሰጥቷል። የአሁን ተጠሪ በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለባህር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍ/ቤት ያቀረበችዉ ሲሆን ፍ/ቤቱም ግራ ቀኙን በማከራከር በሰጠዉ ዉሳኔ የባልና ሚሰት ንብረት በተመለከተ በተወሰኑ ንብረቶች ላይ የሥር ፍ/ቤት ጉዳዩን ድጋሚ አጣርቶ እንዲወስን የመለሰ ሲሆን፣ የሰራተኛ ዕዳ የተባለዉን የሥር ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል።............

Previous Article እነ አቶ ጁሀር ያህያ እና ወ/ሮ መሬም አህመድ የሰ.መ.ቁ 179607
Next Article እነ ወ/ሮ አያልነሽ ፈንቴ እና ወ/ሮ ብርሃኔ ተካ የሰ-መ-ቁ182110
Print
14746

Documents to download