Friday, April 2, 2021 / Categories: CASSATION, Judgement, 2013, Cassation ኢንፎኔት ኮሌጅ ለ የአቶ መንገሻ ታደሰ ወራሽ ወ/ሪት ፍቅርተ መንገሻ የሠ/መ/ቁጥር 198152 ጉዳዩ ለተጠሪ ይመለስ በተባለ ቤት ላይ አመልካች ከወረዳ ኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ጽ/ቤት ጋር ያደረገዉ የቤት ኪራይ ዉል እንዲፈርስ በመወሰኑ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሟል ተብሎ በቀረበ አቤቱታ መነሻ የተደረገ ክርክር የሚመለከት ነዉ፡፡ ተጠሪ በአሁን አመልካች እና በስር 1ኛ ተከሳሽ የአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 ኮንስትራክሽንና ቤቶች ልማት ጽ/ቤት ላይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመሰረቱት ክስ በአዉራሻቸዉ ስም ተመዝግቦ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ክልል ዉስጥ የቤት ቁጥር 1487 የሆነ ይዞታ ላይ የሚገኘዉን ቤት በቀን 26/04/1999ዓ/ም በተደረገ ዉል ለአሁን አመልካች ለ10 ዓመት አከራይተዉ የነበረዉን ቤቱ በአዋጅ ቁጥር 47/1967 ያልተወረሰ ሆኖ እያለ የሥር 1ኛ ተከሳሽ ቤቱን በመንግስት እንደተወረሰ ቤት በማስመሰል የኪራይ ዉሉን በማቋረጥ በቀጥታ ራሱ ከአሁን አመልካች ጋር ከጥር 2009ዓ/ም ጀምሮ የኪራይ ዉል በመዋዋል አከራይቶታል፡፡ Previous Article ሊቢያ ኦይል ኢትዮጵያ ሊሚትድ እና አቶ ዓሊ መሃመድ ፣ወ-ሮ ዘምዘም፣ ወ-ሮ ፎዚያ መሃመድ የሰ-መ-ቁ. 187065 Next Article ዘሀራ ሰዒድ እና የደቡብ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ መዝገቡ ሰ-መ-ቁ 193294 Print 14195 Documents to download ኢንፎኔት ኮሌጅ ለ የአቶ መንገሻ ታደሰ ወራሽ ወ-ሪት ፍቅርተ መንገሻ የሰ-መ-ቁጥር 198152(.pdf, 342.79 KB) - 853 download(s)