/ Categories: CASSATION, Judgement, 2013, Cassation

እነ ሻለቃ ሰብሪ ቶፊቅ መሐመድ እና ሌ/ኮ/ል አለሙ ጌትነት አባተ የሰ-መ-ቁ 183941

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጥር 16 ቀን 2011 በዋለው ችሎት በመዝገብ ቁጥር 72043 የሰጠው ፍርድ እና ውሳኔ እንዲሁም ይህን ፍርድ እና ውሳኔ በማፅናት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰኔ 25 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት የሰጠው ፍርድ እና ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለት በሰበር እንድታረም አመልካች መስከረም 19 ቀን 2011 ዓ/ም ያቀረቡት የሰበር አቤቱታ ያስቀርባል ተብሎ መዝገቡ ለችሎት ቀርቧል። 

ጉዳዩ የተጀመረው በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች በ2ኛ ተከሳሽነት ፣ ተጠሪ በከሳሽነት፣ የኡዴ የጋራ የመኖሪያ ቤት ኃ/የተ/የሕ/ሥራ ማህበር በ1ኛ ተከሳሽነት ፣ የአቃ/ቃ/ክ/ከ/ንግድ እና ኢንደስትሪ ልማት ጽ/ቤት በ3ኛ ተከሳሽነት ተከራክረዋል፡፡ የሥር ከሳሽ በክሳቸው ፣ ቀደም ሲል የኢፌዴሪ አየር ሀይል ጠቅላይ መምሪያ አባል ሆነው ከሌሎች 11 የስራ ባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን የሥር 1ኛ ተከሳሽ የሆነው የኡዴ የጋራ የመኖሪያ ቤት ኃ/የተ/የሕ/ሥራ ማህበር በ1997 ዓ/ም መስርተው የመዋጮ ገንዘብ በዝግ የባንክ ሂሳብ ቁጥር ገቢ አድርገው በአቃቂ ቃሊት ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ክልል ውስጥ ለቤት መስሪያ ቦታ በማህበሩ ስም ተረክበው ፤ ማህበሩ ቦታውን ተረክቦ ወደ ግንባታ ከመግባቱ በፊት ተጠሪ በ2001 ዓ/ም በወንጀል ተከሰው የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው በእስር ላይ እያሉ የቤቱን ጉዳይ እንዲከታተሉላቸው ወንድማቸው አቶ ቢንያም ጌትነትን ወክለው እያለ ፤ ተጠሪ ግዴታቸውን አልተወጡም በማለት የሥር 1ኛ ተከሳሽ ማስጠንቀቂያ ያወጣ ቢሆንም ተወካያቸው ማስጠንቀቂያው ተነስቶ ተጠሪ ግዴታቸውን ተወጥተው በአባልነታቸው እንዲቀጥሉ ያቀረቡትን ጥያቄ እና የሥር 3ኛ ተከሳሽ ድርጊቱ ተገቢ ስላልሆነ ቆሞ በአባልነታቸው እንዲቀጥሉ የጽፉትን ደብዳቤ ባለመቀበል ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎችን በመስጠት ተጠሪ ከአባልነት በማሰናበት አመልካችን መተካቱ ፤ የሥር 3ኛ ተከሳሽም መተካካቱ ተገቢ አለመሆኑን እያወቀ ከሥር 1ኛ ተከሳሽ ጋር ተባባሪ በመሆን በጋዜጣ በማውጣት ተጠሪ መብታቸውን እንዲያጡ ያደረገ በመሆኑ የሥር 1ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች አመልካችን ከማህበሩ አሰናብተው ተጠሪን ወደ አባልነት በመመለስ መብታቸውን እንዲያስከብሩላቸው ጠይቀዋል፡፡……

Previous Article እነ ወ-ሮ ባህጃ ሳላህ፣ወ-ሮ ፎዚያ መሀመድ እና ወ-ሪት ምስራ አግዛ የሰ-መ-ቁጥር 184798
Next Article የእነ አምሳሉ አበራ እና አሻግሬ አበራ የሰ-መ-ቁ195361
Print
14580