/ Categories: CASSATION, Judgement, 2013, Cassation

እነ አቶ ሐይሌ ንማኒ፣አቶ ነስሩ አህመድ፣ጀማል ዋበላ እና ወ/ሪት ምንዳዬ ለገሰ የሰ-መ-ቁ-188293

ጉዳዩ የንግድ መደብር ሽያጭ ውልን መነሻ ያደረገ ክርክር የሚመለከት ሆኖ ክርክሩ በተጀመረበት በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 1ኛ አመልካች 2ኛ ተከሳሽ እና 2ኛ አመልካች ጣልቃ ገብ በመሆን እንዲሁም 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ 2ኛ ተጠሪ ደግሞ 1ኛ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ ከክርክሩ እንደተረዳነዉ 1ኛ ተጠሪ በአሁን 1ኛ አመልካች እና በ2ኛ ተጠሪ ላይ በመሰረቱት ክስ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 08 የቤት ቁጥር 222 የሆነ በንግድ ምዝገባ ቁጥር AA/AK/08/2/1/000075/2006 በቀን 20/08/2002 የተመዘገበ እና በቀን 11/07/2006 ዓ/ም በቁጥር 14/671/710375/2006 የንግድ ፍቃድ የወጣበት የትራንስፖርት ፣የመጋዘንና የኮሚኒኬሽን ስራዎች ንግድ የሚካሄድበት የንግድ መደብር 1ኛ ተጠሪ በቀን 13/07/2006 ዓ/ም በብር 400,000.00 ለመግዛት ተስማምተው ቅድመ ክፍያ ብር 50‚000.00 ለ2ኛ ተጠሪ ከፍለዉ ቀሪውን ክፍያ 2ኛ ተጠሪ የንግድ መደብሩን ከተለያዩ ግዴታዎች አፅድተው ከነሰነዱ ሲያስረክቡ ለመቀበል ተስማምተዋል፡፡ሆኖም 2ኛ ተጠሪ እንደ ውሉ ግዴታቸውን ያልተወጡ በመሆኑ የንግድ መደብሩ በአሁን 1ኛ አመልካች እጅ የሚገኝ በመሆኑ የንግድ መደብሩን ለአሁን 1ኛ ተጠሪ እንዲያስረክቡ እና የአሁን 2ኛ ተጠሪ እንደ ውሉ ባለመፈፀማቸው ብር 50‚000.00  እንዲከፍሉ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡………..

Previous Article ወ-ሮ አበባዬ ጌቶ እና ወ-ሮ ወርቅዬ ጌቶ የሰ-መ-ቁ 187253
Next Article አቶ ደምሴ ኦዳ ከ አቶ አሰፋ ወርቁ
Print
16101