/ Categories: CASSATION, Cassation

እነ አቶ አበራ ነጋሽ ደምሴ(6) ሰዎች እና ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን፤ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ፅ/ቤት የሰበር መ/ቁ/245981

ጉዳዩ የመሬት ባለይዞታነት መብት የሚመለከት ሲሆን በስር ፍርድ ቤት የአሁን አመልካቾች ከሳሽ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡አመልካቾች በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመ/ቁ131415 ባቀረቡት ክስ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል ውስጥ የሚገኝ ከ1-5 የተዘረዘሩት አመልካቾች ወላጅ አባት እና የ6ኛ አመልካች ወንድም የሆኑት በጋራ ይዘው ይጠቀሙበት የነበረ በግምት ከ60‚000 ካ.ሜ ያላነሰ ስፋት ያለው አዋሳኞቹ በክሱ የተጠቀሰ ይዞታ ለረጅም ጊዜ ግብር እየገበሩበት ሲጠቀሙ የቆዩ ቢሆንም ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በ1ኛ ተጠሪ ቤተክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ኮሚቴ አባላት አማካኝነት የሀይማኖት ተቋሙ በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን መፈራት እና መከበር በመጠቀም የአመልካቾችን ይዞታ ለመቃብር ቦታ በሚል ምክንያት በመውሰድ ከፋፍሎ እና ሼዶችን ገንብቶ ለጋራዥ እና ሌሎች የንግድ አገልግሎቶች ኪራይ ገቢ እየሰበሰበ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲሰራ በማድረግ በህገወጥ መንገድ ይዞት ይገኛል፡፡ስለሆነም ለ1ኛተጠሪ የተሰጠው የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተሰርዞ ለአመልካቾች እንዲመለስ ሲሉ ዳኝነት መጠየቃቸዉን መዝገቡ ያሣያል፡፡መልካም ንባብ….

Print
3570

Documents to download

  • 245981(.pdf, 942 KB) - 543 download(s)