/ Categories: CASSATION, Judgement, 2013, Cassation

እነ ወ-ሮ ሐመልማል ታመነ ወ-ሮ የምስራች ተካ እና አቶ ክፍሌ ተካ የሰ-መ -ቁ 184335

አመልካች ጥቅምት 3 ቀን 2012 ዓ/ም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ የደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 07508 ሐምሌ 26 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚው ችሎት በመዝገብ ቁጥር 07390 ግንቦት 15 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት የሰጠውን ፍርድ እና ውሳኔ ማፅናቱ መሠረታዊ የህግ ስህተት ነው በማለት በሰበር ለማሳረም ያቀረቡትን ቅሬታ ለመመርመር መዝገቡ ለችሎት ቀርቧል።ጉዳዩ የውርስ ንብረት እንዲጣራ የቀረበ ክርክር ሆኖ ክርክሩ በተጀመረበት የሼይ ቤንች ወረዳ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች በከሳኝነት ፣ በሰበር ክርክሩ የሌሉት አቶ ፍቃዱ ተካ በተከሳሽነት እና አመልካች እና ሌሎች በሰበር ክርክሩ ተካፋይ ያልሆኑት 3 ሰዎች በጣልቃ ገብነት ተከራክረዋል። 1ኛ ተጠሪ ያቀረቡት የውርስ ይጣራ አቤቱታ ከሥር ተከሳሽ ጋር ከሟች አቶ ተካ ከበደ የሚወለዱ መሆኑንና አባታቸው ጳጉሜ 1 ቀን 2009 ዓ/ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ገልጸው በህይወት በነበሩበት ወቅት በሚዛን ከተማ ህብረት ቀበሌ ኮንዶሚንዬም ፊት ለፊት ከመንገድ በታች ያለው አንድ ክፍል ቤት ከይዞታው ጭምር እንዲሁም ሌሎች በሟቹ የተፈሩ ናቸው የሚሉትን ንብረቶችን በመዘርዘር የውርስ ንብረቶቹን ሌሎች በእጃቸው ይዘው የሚገለገሉበት መሆኑን ገልፀው ድርሻቸውን ማግኘት እንዲችሉ የውርስ አጣሪ ተሹሞ የውርስ ሀብቱ እንዲጣራ ፣ ወራሾች እንዲለዩ እና ንብረቶቹ በአጣሪው እንድተዳደሩ እንድወሰን አመልክቷዋል። የሥር ተከሳሽ ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ውድቅ መሆኑን መዝገቡ የሚያስረዳ ሲሆን በአማራጭ በፍሬ ነገሩ ላይ ባቀረቡት መልስም በክሱ ውስጥ መብት እና ጥቅም ያላቸው አመልካች እና ሌሎች ሰዎች ስላሉ በፍርድ ቤቱ ጥር ወደ ክርክሩ እንዲገቡ ፤ የውርስ አጣሪ እንዲሾም ፤ የውርስ ንብረቱ የወራሾች የጋራ ሆኖ በሟች በመታሰቢያነት በቅርስነት እንዲቆይ ፤ ለሟች ተስካር ፣ የሙት ዓመት እና ሌሎች ወጪዎች እንድሁም ዕዳም ካለ እንድጣራ ጠይቋል። አመልካች እና ሌሎች ከውርስ ሀብቱ መብት አለቸው የተባሉትን አራት ሰዎች በፍርድ ቤቱ ጥሪ ወደ ክርክሩ ገብተው ከሥር ተከሳሽ ጋር የሚመሳሰል መልስ መስጠታቸውን ፍርድ ቤቱ  መዝግቧል። ፍርድ ቤቱ የውርስ አጣሪ የሾመ ቢሆንም የሟች ውርስ ሀብት በአግባቡ አልተጣራም በማለት ሪፖርቱ ውድቅ በማድረግ ግራ ቀኙ ወደ ክርክሩ እንድገቡ አድርጓል። የሥር ተከሳሽ በሚዛን ከተማ ህብረት ቀበሌ ኮንዶሚንየም ሰፈር ያለው ቤት በሟች ስም አለመመዝገቡ ፣ የሟች ቀለበቶች በእሱ እጅ አለመኖራቸውን ፣ ለሟች አርባ እና የተለያዩ ወጪዎች ተጣርተው ቀርበው ክፍፍል እንድደረግ ጠይቋል። ጣልቃ ገቢዎችም ተመሳሳይ ክርክር ማቅረባቸው በፍርዱ ላይ የተመላከተ ሲሆን የሥር ከሳሽም በጽሁፍ ክርክራቸው የጠየቁትን ዳኝነት በማንሳት መከራከራቸው ተመላክቷል።……….

Previous Article አቶ ግደይ ገ-ጻድቃን ገ-ማርያም እና ወ-ሮ ክንድሀፍቲ ኢታይ የሰ-መ-ቁ 179589
Next Article እነ ወ-ሮ ፈይዛ ከማል አወል፣አቶ አብዲ አህመድ መሀመድ እና አቶ ካህሳይ ተስፋዝጊ የሰ-መ-ቁ 184601
Print
13300