/ Categories: CASSATION, Cassation

ወ/ሮ ሙርሽዳ ሁሴን እና ወ/ሮ አልፊያ ሁሴን (13) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 257243

ጉዳዩ የውርስ ንብረት እና የሚስትነት ድርሻ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ጉዳዩ በጀመረበት በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ስልጤ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የአሁን አመልካች 1ኛ ጣ/ገብ ፤ከ1ኛ እስከ 5ኛ ያሉ ተጠሪዎች ከሳሽ፤ከ6ኛ እስከ 13ኛ ያሉ ተጠሪዎች እንዲሁ ጣ/ገብ አመልካች ነበሩ፡፡ አሁን ከ1ኛ እስከ 5ኛ ያሉ ተጠሪዎች አሁን በክርክሩ በሌሉ ሁለት ተከሳሾች ላይ ባቀረቡት ክስ የሟች አባታቸው አቶ ሁሴን አህመድ ንብረት የሆኑና በሟች ስም የሚገኙ 1ኛ/ በስር 1ኛ ተከሳሽ እጅ የሚገኝ በአሊቾ ውሪሮ ወረዳ ቀረሶ ቀበሌ ገሸዴ ተብሎ በሚጠራ መንደር የሚገኝ 3 ጥማድ የእርሻ መሬት፤2ኛ/ በስር 2ኛ ተከሳሽ እጅ የሚገኝ በወልቂጤ ከተማ 01 ቀበሌ የሚገኝ በ1050 ካ.ሜ ላይ ያለ የንግድ ቤት እና ከቤቱ የሚገኝ የኪራይ ገቢ፤3ኛ/ በስር 1ኛ ተከሳሽ እጅ የሚገኝ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 03-21138 የሆነ ዶልፊን ተሽከርካሪ፤ 4ኛ/ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና በደቡብ ግሎባል ባንክ በሟች ስም በተከፈቱ ሂሳቦች የተቀመጠ ገንዘብ የሟች የውርስ ሀብት ስለሆነ በድርሻችን ተከሳሾች ያካፍሉን ሲሉ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…

Print
4919

Documents to download

  • 257243(.pdf, 868.34 KB) - 736 download(s)