/ Categories: CASSATION, 2013, Cassation

ወ/ሮ ፍሬሕይወት ይልማ እና ፋና ቦሌ ሸማቾች ኃ/የተ/የሕብረት ሥራ ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 216200

የክርክሩን አመጣጥ ከሥር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው አመልካች በሥር ፍርድ ቤት ከሳሽ፤ ተጠሪ ተከሳሽ ነበሩ፡፡ አመልካች ሕዳር 30 ቀን 2013 ዓ/ም በተጻፈ ክስ በተጠሪ ማሕበር በምግብና መጠጥ ቁጥጥር ዋና ክፍል ኃላፊነት የሥራ መደብ ተቀጥሬ ስሰራ ከሕግ ውጭ የሥራ ውሌን በማቋረጡ በሕብረት ሥራ ማሕበራት ሕግና በተጠሪ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በሽምግልና ዳኞች እንዲታይ ዳኛ ለማስመረጥና ለማስመደብ ክስ አቅርቤ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 94768 ግንቦት 15 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት ጉዳዩ በሽምግልና ዳኞች ሳይሆን በሥራ ክርክር ችሎት ነው የሚታይ በማለት ክሱን ውድቅ አድርጓል፡፡ ጉዳዩ በይግባኝ ሆነ በሰበር ችሎት ተቀባይነት ያላገኘ በመሆኑ የሥራ ክርክር ችሎት ክሴን ተቀብሎ ወደሥራ እንድመለስ እንዲወሰንልኝ፣ ተጠሪ ለመመለስ ፈቃደኛ ካልሆነ ካሣ፣ የሥራ ስንብት ክፍያ፣ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ክፍያ፣ ክፍያ ለዘገየበት ቅጣት፣ የዓመት ዕረፍት ክፍያ፣ በ2006 ዓ/ም የሐምሌ ወር ደመወዝ፣ በ2006 ዓ/ም የቡና ገለባ ሽያጭ በሕብረት ሥምምነቱ መሠረት ሊከፈለኝ የሚገባ ብር 1,900.00 እንዲከፈለኝ፣ የሥራ ምስክር ወረቀት እንዲሰጠኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ አመልካች ባቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አመልካች የሥራ መሪ በመሆናቸው ክሱ በሥራ ክርክር ችሎት ሊታይ አይገባም፣ ክሱ በይርጋ ቀሪ ነው በማለት ተከራክሯል፡፡መልካም ንባብ…..

Print
10075

Documents to download

  • 216200(.pdf, 1.07 MB) - 886 download(s)