/ Categories: CASSATION, Cassation

የቂ/ክ/ከተማ ወረዳ 10 ቤቶች አስተዳደር ጽቤት እና የኢትዮጵያና ጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት ሰ/መ/ቁ፡-197405

ለዚህ የሰበር ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ ሊቀርብ የቻለው አመልካቾች ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በተፃፈ ማመልከቻ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመ/ቁ. 247606 ግንቦት 17 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት የስር ፍርድ ቤትን ውሳኔ በማፅናት የሰጠው ትዕዛዝ መሰረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈፀመበት መሆኑን ገልፀው በሰበር ችሎት ታይቶ ይታረምልኝ በማለት ባቀረቡት ማመልከቻ መነሻነት ነው፡፡አመልካቾች በስር በፌደራል መጀመሪያ ደረጀ ፍርድ ቤት ተከሳሾች የነበሩ ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ ነበር፡፡

ተጠሪ በስር ፍርድ ቤት በአመልካቾች ላይ ባቀረበው ክስ ተጠሪ በኢትዮጵያ ጅቡቲ መንግስት መካከል በተደረገው ዓለም አቀፍ ስምምነት መሰረት በተቋቋመ የሁለቱ መንግስታት ንብረት የሆነ የዓለም አቀፍ ድርጅት ሲሆን በሁለቱ መንግስታት የመሬት ይዞታ ተለክቶ ተሰጥቶታል፡፡በአዋጅ ቁ. 47/67 አንቀጽ 43 እና 5 (3) መሰረት የዓለም አቀፍ ድርጅት ቦታ የማይወረስ ሲሆን የተጠሪ ቤትና ይዞታ ያልተወረሰ መሆኑን የሚያረጋግጥ ደብዳቤም በወቅቱ ከነበረው የከተማ ልማትና ቤት ሚኒስቴር ተሰጥቶታል፡፡……………

Print
11841

Documents to download

  • 197405(.pdf, 826.18 KB) - 854 download(s)