Friday, March 4, 2022 / Categories: CASSATION, Cassation የአማራ ክልል ገቢዎች ቢሮ ዐቃቤ ህግ ዓ/ህግ እና ደሳለኝ ቸኮል የሰ/መ/ቁ.201365 በዚህ መዝገብ ላይ የቀረበው ጉዳይ ያለደረሰኝ እና የጭያሽ መመዝገቢያ ማሽን ግብይት መፈፀም ወንጀልን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው አመልካች በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ደቡብ ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአሁን ተጠሪን ጨምሮ በሁለት ሰዎች ላይ ባቀረበው ክስ ነው፡፡ በቀረበው ክስ ላይ ተጠሪ ሁለተኛ ተከሳሽ ነበር፡፡ የቀረበው ክስ ጭብጥም ተከሳሾቹ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 አንቀጽ 120(1) እና 128 ድንጋጌን በመተላለፍ የስር 1ኛ ተከሳሽ የድርጅቱ ባለቤት ሆኖ የአሁን ተጠሪ ደግሞ በድርጅቱ ውስጥ የመስተንግዶ ሰራተኛ ሆኖ እየሰራ እያለ ታህሳስ 16/2012 ዓ.ም ከቀኑ 6፡50 ሰዓት አካባቢ ሁለቱ የዐቃቤ ህግ ምስክሮች እያንዳንዳቸው ለተጠቀሙት ሁለት ሁለት ቢራ ደረሰኝ ሳይሰጣቸው የአሁን ተጠሪ ሂሳብ የተቀበላቸው በመሆኑ ያለደረሰኝ ግብይት ፈፅመዋል፤ በዚህም ውስጥም የአሁን ተጠሪ አስተናጋጅ ሆኖ ዳረሰኝ ሳይሰጥ ሂሳብ በመቀበል ወንጀሉ እንዲፈፀም የስር 1ኛ ተከሳሽን ረድቷል የሚል ነው፡፡……… Print 11885 Documents to download 201365(.pdf, 806.47 KB) - 864 download(s)