Login
  • Register
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • Message from the President
    • History and Traditions
    • Vision Mission and Mandate
    • President
      • Current President
      • Former Presidents
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • Judges
      • Current
      • Former Judges
    • Judicial Administration Council
    • Court Administration & Directorates
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • E-Filing
    • Quick Start Guide
      • Registration
      • E-Filing
    • User Guide
    • Rules and Guidelines
    • Forms
    • Tutorials
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
የየካ ክ/ከተማ ዐቃቤ ህግ ፅ/ቤት እና እነአቶ ብሩክ ወንድሙሰ/መ/ቁ፡-204866

የየካ ክ/ከተማ ዐቃቤ ህግ ፅ/ቤት እና እነአቶ ብሩክ ወንድሙሰ/መ/ቁ፡-204866

ለዚህ የሰበር ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ ሊቀርብ የቻለው አመልካች መጋቢት 20 ቀን 2013 ዓ.ም በተፃፈ የሰበር አቤቱታ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአመልካችን በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.358 የቀረበን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ የሰጠውን ውሳኔ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ከውጤት አንፃር ማፅናቱ መሰረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈፀመበት በመሆኑ ይኸው እንዲታረምልኝ በማለት ያቀረበውን አቤቱታ መነሻ በማድረግ ሲሆን አመልካች በስር ፍርድ ቤት የመ/አመልካች የነበረ ሲሆን ተጠሪዎች የመ/ተጠሪዎች ነበሩ፡፡አመልካች በስር ፍርድ ቤት በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.358 መሰረት ባቀረበው አቤቱታም አመልካች በአዋጅ ቁጥር 64/2011 መሰረት የአስተዳደሩን እና የነዋሪዎችን መብት እና ጥቅም በማስከበር በማናቸውም የዳኝነት አካል ዘንድ የመቃወም አቤቱታ የማቅረብ መብት እንዳለው በመግለፅ በመቃወም ተጠሪዎች እና በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 7 አስተዳደር ፅ/ቤት መካከል በተደረገው ክርክር ላይ ፍርድ ቤቱ የሰጠው ውሳኔ መብቴን የሚነካ በመሆኑ ሊሰረዝ ይገባል በማለት አመልክቷል፡፡………………….

ኮ/ል ተክለብርሃን ገ/መድህን እና የደ/ዕዝ ወታደራዊ ዓ/ህግ የሰ/መ/ቁ፡- 204813እና206556

ኮ/ል ተክለብርሃን ገ/መድህን እና የደ/ዕዝ ወታደራዊ ዓ/ህግ የሰ/መ/ቁ፡- 204813እና206556

ክርክሩ የተጀመረው የአሁን ተጠሪ  መስከረም 4 ቀን 2013 ዓ.ም  በአመልካቾች ላይ በኢፌዲሪ የቀዳሚ ወታደራዊ ፍ/ቤት ባቀረበው የመጀመሪያ ክስ አመልካቾች የመከላከያ ሰራዊት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1100/2011 አንቀጽ 2 (12)፣ የኮቪድ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር በወጣው አስቸኳይ አዋጅ ቁጥር 3/2012  በወንጀል ህግ አንቀጽ 32/1/ሀ እና 298/2/ የተደነገገውን  በመተላለፍ  ሰኔ 23 ቀን 2012 በግምት ከምሽቱ 3፡30 ሲሆን የተደራጁ ህገወጥ ቡድኖች ገጀራ ፣ፌሮ ብረትና ዱላ በመያዝ በሻሸመኔ ከተማ የህብረተሰቡን ንብረት እያቃጠሉ እያወደሙና እየዘረፉ በመሆኑ በክፍሉ አመራር ሜ/ር ጀኔራል ሹማ አብዴታ በስልክ ይህንን ህገወጥ ተግባር ተመጣጣኝ እርምጃ በመውሰድ እንዲቆጣጠሩ እና ህብረተሰቡን እንዲታደጉ የሰጣቸውን ትዕዛዝ በመጣስ ትዕዛዙን ሳይፈጽሙ ቀርተዋል በማለት የከሰሰ ሲሆን፤በሁለተኛው ክስም አመልካቾች የመከላከያ ሰራዊት ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1100/2011 አንቀት 2/12፣ የኮቪድ ወረርሽኝ ለመቆጣጠር በወጣው አስቸኳይ አዋጅ ቂጥር 3/2012 እና በኢፌዲሪ ወንጀል ህግ ቁጥር 32/1/ሀ እና 293/2/ የተደነገገውን በመተላለፍ፣ በ1999 ዓ.ም የወጣውን የመከላከያ ሰራዊት ቋሚ የግዳጅ አፈጻጸም ደንብ ቁጥር መከ-002/1999 ተ.ቁ 6.3 እና 7.5 መሰረት ሰራዊቱ ማናቸውም ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ አደጋዎች ሲደርሱ አደጋውን ለማስቆም ተመጣጣኝ እርምጅ በመውሰድ ህዝቡን ከአደጋ መታደግ እንዳለበት በግልጽ ተደንግጎ እያለ በተደራጁ ህገወጥ ቡድኖች የህብረተሰቡ ህይወት አደጋ ላይ ሲወድቅ ንብረት በከፍተኛ ሁኔታ ሲዘረፍ ሲቃጠል የስር  አመልካቾች ግዳጅ ላይ እያሉ በመከላከያ ሀይሎች የአገልግሎት ደንብ መሰረት ተመጣጣኝ እርምጃ በመውሰድ ህብረተሰቡን ከአደጋ ባለመታደጋቸው ጉዳት ሊደርስ ችሏል  በማለት ክስ መስርቶባቸዋል፡፡……………….

ታጁዲን እንድሪስ እና እነ እንድሪስ ሰይድ የሰ/መ/ቁ፡- 204608

ታጁዲን እንድሪስ እና እነ እንድሪስ ሰይድ የሰ/መ/ቁ፡- 204608

 ጉዳዩ የይዞታ ክርክርን የሚመለከት ሆኖ ለዚህ ውሣኔ ምክንያት የሆነው የአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 03-30456 ጥር 3ቀን 2013ዓ/ም በዋለው ችሎት ቀደም ሲል በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ተጣርቶ የቀረበለትን ጉዳይ በመለወጥ እንደገና ተጣርቶ እንዲወሰን ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ስር ፍርድ ቤቱ መመለሱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ተብሎ እንዲወሰንላቸው አመልካቾች ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ መነሻነት ነው፡፡…….

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን እና እነ ዶ/ር በድሩ ሁሴን የሰ /መ/ቁ፡- 204300

የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን እና እነ ዶ/ር በድሩ ሁሴን የሰ /መ/ቁ፡- 204300

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች መጋቢት 10 ቀን 2013 ዓ.ም ጽፎ ባቀረበው የሰበር አቤቱታ የፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመ.ቁ 268995 በቀን 22/12/2012 ዓ.ም አመልካች በመንገድ ሥራ ምክንያት የፈጠረው የሁከት ተግባር እንዲወገድ ሲል የሰጠው ውሳኔ፤ ይህንኑ ውሳኔ በማጽናት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 259606 በቀን 19/06/2013 ዓ.ም የሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረባቸው ነው፡፡…………….

ወ/ሮ ረሂማ አብዱላሂ እና እነ ከዲር ዮሱፍ በከር የሰ/መ/ቁ፡- 202581

ወ/ሮ ረሂማ አብዱላሂ እና እነ ከዲር ዮሱፍ በከር የሰ/መ/ቁ፡- 202581

ጉዳዩ የጋራ የሆነ የእርሻ መሬት በሽያጭ ለማስተላለፍ የተደረገ ነዉ የተባለዉ ዉል ቀሪ እንዲደረግና ይዞታዉን ለማስለቀቅ እንዲሁም አላባ ለማስከፈል የቀረበ ክስ የመዳኝት ሥልጣን የሚመለከት ነዉ፡፡ አመልካች በተጠሪዎችና በስር 1ኛ ተከሳሽ አቶ ሙስጠፋ ዩሱፍ ላይ በሐረሪ ክልል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመሰረቱት ክስ ከስር 1ኛ ተከሳሽ ጋር ለ30 ዓመታት በትዳር ተሳስረን አብረን ስንኖር በሐረር ክልል በድሬ ጠያራ ወረዳ በአቦከር ሙጢ ቀበሌ ገበሬ ማኅበር ዉስጥ ያለንን አንድ ጥማድ ከግማሽ የሆነ አዋሳኙ በክሱ የተጠቀሰዉን የእርሻ መሬት ያለእኔ ፈቃድ በሕገ-ወጥ መንገድ ለአሁን ተጠሪዎች በሽያጭ አስተላልፈዋል፡፡ በዚህ ምክንያት በአመት 20 ኩንታል ማሽላ በማምረት ማግኘት የምንችለዉን በኩንታል በብር 1200.00 ሂሳብ ብር 24,000.00 አሳጥዉኛል፡፡እየተቃወምኩ በመሬቱ ላይ ተጠሪዎች ቤት ሰርተዉበታል፡፡ስለሆነም ዉሉ ሕገ-ወጥ ስለሆነ እንዲፈርስና የገነቡትን ቤት አፍርሰዉ ይዞታዬን እንዲለቁ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡……………

FirstPrevious891011121314151617NextLast
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us 
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions