አቶ አዲሱ ዓለሙ እና ወ/ሮ መስከረም ንጉሴ የሰ/መ/ቁ፡- 202486

አቶ አዲሱ ዓለሙ እና ወ/ሮ መስከረም ንጉሴ የሰ/መ/ቁ፡- 202486

የሰበር መዝገቡ የቀረበው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው አመልካች የስር ተከሳሽ ሲሆኑ ተጠሪ ከሳሽ ነበሩ፡፡ ተጠሪ ያቀረቡት ክስ የአመልካች ሚኒባስ መኪና በሆነ ተሳፍረን በምንጓዝበት ጊዜ ከቆመ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ በቀኝ እግሬ የታፋ አጥንት እና በግራ እግሬ ከጉልበት በታች አጥንት ስብራት በመድረሱ 28% ቋሚ አካል ጉዳት ደርሶብኛል፡፡ የጉዳት ካሣ ብር 406,230.00፣ የሕክምና ወጪ ብር 90,770.00፣ የአልሚ ምግብ ወጪ ብር 2,000.00 እና የሞራል ካሣ ብር 1,000.00 በድምሩ ብር 500,00.00 አመልካች እንዲከፍሉ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ አመልካች የሠጡት መልስ በንግድ ሕጉ መሠረት በውል ስትጓዝ ነው ጉዳቱ የደረሰው፣ የቀረበው የጉዳት መጠን የተጋነነ የሚል ሲሆን ለመኪናው የመድን ሽፋን የሠጠው መድን ድርጅት ጣልቃ ገብቶ እንዲከራከር ጠይቀዋል፡፡……………

ማክሼቭ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና ወጋገን ባንክ አክሲዮን ማህበር የሰ/መ/ቁ፡-201990

ማክሼቭ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና ወጋገን ባንክ አክሲዮን ማህበር የሰ/መ/ቁ፡-201990

ጉዳዩ የብድር ውል ይፍረስልኝ በሚል የቀረበ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ጉዳዩ በተጀመረበት የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡

አመልካች ታህሳስ 18 ቀን 2012 ዓ.ም በተፃፈ ክስ ከተጠሪ ጋር ሚያዝያ 11 ቀን 2011 ዓ.ም በተደረገ የብድር ውል ስምምነት ብር 2,631,246.08 መበደሩን፣ አከፋፈሉም ውሉ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ በየሶስት ወሩ ሁኖ ወለድና የተለያዩ ወጪዎችን ጨምሮ ብር 349,124.00 መሆኑንና በ8 ጊዜ ክፍያ በ2 ዓመት ውስጥ እስከ ሚያዝያ 11 ቀን 2013 ዓ.ም ተከፍሎ እንዲጠናቀቅ መስማማታቸውን ነግር ግን ተጠሪ ክፍያው በ7 ጊዜ እንዲጠናቀቅ ማድረጉን፤ ይህም የሒሳብ መዝገብ አያያዝ ላይ ችግር መፍጠሩን፤ የወለድ መጠኑ ላይም ከፍተኛ ልዩነት በማምጣት የተስተካከለ የኦዲት ሪፖርት እንዳይኖር እክል መፍጠሩን፤ በዚህም ምክንያት አመልካች የ2012 ዓ.ም የግብር ክሊራንስ አግኝቶ የንግድ ፍቃዱን ለማሳደስ አለመቻሉን እና ተጠሪም ይህን ለማስተካከል ፍቃደኛ አለመሆኑን ጠቅሶ የብድር ውሉ እንዲፈርስ ዳኝነት ጠይቋል፡፡…………

አቶ ታደሰ ንጉሴ እና አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ሻሸመኔ ቅርንጫፍ የሠ/መ/ቁጥር 201974

አቶ ታደሰ ንጉሴ እና አዋሽ ኢንተርናሽናል ባንክ ሻሸመኔ ቅርንጫፍ የሠ/መ/ቁጥር 201974

ጉዳዩ የሥራ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን አመልካች በኦሮሚያ ክልል በሻሸመኔ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በተጠሪ ላይ በመሰረቱት ክስ ከተጠሪ ጋር በ1989 ዓ/ም በፈፀሙት የስራ ውል በባላንስ ሠራተኛነት የስራ መደብ ላይ በወር 13,034.00 እየተከፈላቸዉ እንዲሰሩ ተቀጥረዉ ሲሰሩ መቆየታቸዉን፤ነገር ግን ያለምንም ምክንያት በቀን 07/09/2011ዓ/ም በተጻፈ ደብዳቤ የትራንዛክሽን ሥራ በመስራት በማሳለፍ ብድር በመዝጋት ባንኩ ማግኘት ያለበትን በማሳጣት ጥፋት ፈጽመሀል በማለት ሥራዬ ትራንዛክሽን ማሳለፍ ባለመሆኑ የሰራሁት ጥፋት ሳይኖር ከሕግ-ዉጭ ከሥራ አሰናብቶኛል፡፡ስለሆነም ወደ ሥራ እንዲመልሰኝ እንዲወሰንልኝ፡፡ይህ የሚታለፍ ከሆነ የስንብት ክፍያ ብር 95,582.67 ፣የ15 ቀን ደመወዝ ብር 6,517.00 ፣ክፍያ ለዘገየበት የሶስት ወር ደመወዝ ብር 39,102.00 ፣ካሳ የ6 ወር ደመወዝ ብር 78,204.00፣የፕሮቪደንት ፈንድ ክፍያ ብር 63,550.29፣ተጠሪ ባንክ በመተዳደሪያ ደንቡ መሰረት ከ20 ዓመት በላይ ላገለገለ ሰራተኛ 21 ካራት ወርቅ ስለሚሰጥ የዚህ ዋጋ የአንድ ካራት ዋጋ ብር 1,700.00 ብር 35,700.00፣የቦነስ ክፍያ የ2011 ዓ/ም ብር 39,102.00፣ከ2009-2011ዓ/ም ድረስ ያልተጠቀምኩበትን የሶስት ዓመት  የአመት እረፍት ወደገንዘብ ቀይሮ እንዲከፍለኝ በአቃላይ ብር 370,991.29 (ሶስት መቶ ሰባ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አንድ ብር ከሃያ ዘጠኝ ሳንቲም) እንዲከፈላቸዉ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡…………….

 

 

አቶ ሆርዶፋ ዴቲ እና ወ/ሮ ፀሐይ ሽፈራው የሰ/መ/ቁ፡-201929

አቶ ሆርዶፋ ዴቲ እና ወ/ሮ ፀሐይ ሽፈራው የሰ/መ/ቁ፡-201929

ጉዳዩ የፍርድ አፈፃፀም ክስ መነሻ ያደረገ ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው ኦሮሚያ ክልል ጅማ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የአሁን 1ኛ ተጠሪ የአፈጻጸም ከሳሽ፤የአሁኑ አመልካች በአፈጻጸም ተከሳሽ፤የአሁኑ 2ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ጣልቃ ገብ በመሆን ተከራክረዋል፡፡የክርክሩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ አመልካች እና 1ኛ ተጠሪ ጋብቻቸው በፍቺ እንዲፈርስ ከተወሰነ በኋላ 200 ሄክታር የቡና ልማት የኢንቨስትመንት ይዞታ የጋራ ንብረት ነዉ ተብሎ እኩል እንዲካፈሉ ተወስኖ የፌዴራል ፍ/ቤቶች የአፈፃፀም ዳይሬክቶሬት ንብረቱ ያለበት የጅማ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በውክልና ውሳኔውን እንዲያስፈጽም ትዕዛዝ መስጠቱን ተከትሎ የአፈፃፀም መዝገብ ቁ/42899 ተከፍቶ በሂደት ላይ እያለ 2ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎች በየበኩላቸዉ ባልና ሚስቱ ከባንኩ ተበድረዉ ያልከፈሉት እዳ መኖሩን በተለያየ መዝገብ ያሰጡትን ፍርድ በማቅረብ ንብረቱ በባልና ሚስት መካከል ክፍፍል ከመደረጉ በፊት እዳዉ እንዲከፈላቸዉ አቤቱታ በማቅረብ የክርክሩ ተካፋይ መሆናቸዉን መዝገቡ ያሣያል፡፡……………….

 

ወ/ሮ መሠረት ኃይሉ እና ወ/ሮ ቢቂልቱ በየነ የሰ/መ/ቁ. 201128

ወ/ሮ መሠረት ኃይሉ እና ወ/ሮ ቢቂልቱ በየነ የሰ/መ/ቁ. 201128

 ጉዳዩ የፍርድ አፈፃፀምን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በቡራዩ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ተጠሪ የፍርድ ባለመብት በመሆን የፍርድ ባለዕዳ በሆኑት በአመልካች እና ሌሎች ሁለት ግለሰቦች ላይ ባቀረቡት አቤቱታ የቡራዩ ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት በመ/ቁጥር 64593 ላይ በቀን 10/08/2009 ዓ.ም በዋለዉ ችሎት በሰጠዉ ውሳኔ መሠረት እንዲፈፀምላቸው የጠየቁትን ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ፡፡………………

First910111214161718Last