አቶ ብርሃኑ ታደሰ እና የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ቤቶች አስተዳደር ፅ-ቤት የሠ-መ-ቁጥር 190440

አቶ ብርሃኑ ታደሰ እና የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ቤቶች አስተዳደር ፅ-ቤት የሠ-መ-ቁጥር 190440

ጉዳዩ የመንግስት(የቀበሌ) ቤት የመከራየት መብት የሚተላለፍበትን አግባብ በተመለከተ የተሰጠ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነዉ ተብሎ የቀረበ አቤቱታ የሚመለከት ነዉ፡፡ ክርክሩ በተጀመረበት በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አመልካች በተጠሪ ላይ በመሰረቱት ክስ በወ/ሮ ሀረገወይን በላይነህ የማነህ ተከራይተዉ በያዙት በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 በቤት ቁጥር 222 በሆነው ቤት ዉስጥ ከ1975 ዓ/ም ጀምሮ የስድስት ዓመት ህፃን እያለሁ ጀምሮ  እንደልጅ እያስተማሩኝ ያሳደጉኝ እና እስከአሁን ድረስ በቤት ውስጥ በመኖር ላይ እገኛለሁ፡፡ ነገር ግን አሳዳጊዬ የነበረችው ወ/ሮ ሀረገወይን በላይነህ በ1989 ዓ/ም አብረን ከምንኖርበት ቤት እኔ በማላውቀው ምክንያት ከቤት ከወጣች በኋላ አግኝቻት የማላውቅ መሆኔን በመግለፅ የመጥፋት ውሳኔ እንዲሰጠኝ ለአዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት አቤቱታ አቅርቤ ጉዳዩ እየታየ ይገኛል፡፡ የቤቱን ኪራይ በእሷ ስም እየከፈልኩ የምገኝ በመሆኑ በመመሪያ ቁጥር 4/2009 አንቀፅ 15/1 መሰረት የቤቱን ኪራይ ዉል በስሜ እንዲያዋውለኝ ባመለክትም ተጠሪ ሊያስተናግደኝ ፍቃደኛ አልሆነም፡፡ ስለሆነም ተጠሪ የኪራይ ውል እንዲያዋውለኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡……… 

እነ ሳባ አርአያ እና ወ-ሮ ወ-ሮ በሻዱ ያደቴ የሰ-መ-ቁ 182692

እነ ሳባ አርአያ እና ወ-ሮ ወ-ሮ በሻዱ ያደቴ የሰ-መ-ቁ 182692

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካቾች ነሐሴ 17 ቀን 2011 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 299179 ግንቦት 27 ቀን 2011 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረባቸው ነው፡፡

ጉዳዩ የሁከት ይወገድልኝ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በፊንፊኔ ዙሪያ ኦሮሚያ ልዩ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን አመልካቾች ከሳሾች፣ የአሁን ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሾች ነበሩ፡፡ አመልካቾች በስር ፍ/ቤት ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ፡- የአመልካቾች እናት ወ/ሮ ዝናሽ ኪዳኔ በሰበታ ከተማ ቀበሌ 04 ጎጥ 6 ውስጥ የሚገኝ እና አዋሳኙ በክሱ የተገለጸ ስፋቱ 500 ካ.ሬ በሆነው መሬት ላይ የተሰራ ቁጥሩ 9251 የሆነ መኖሪያ ቤት የነበራቸው መሆኑን፤ የአመልካቾች እናት ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ተጠሪዎቹ በቀን 25/03/2010 ዓ.ም ከአመልካቾች ፍላጎት ውጪ የቤቱን አጥር አፍርሰው በመግባት በቤት ውስጥ ያሉትን ሰዎች በጉልበት አስወጥተው ሁከት የፈጠሩባቸው መሆኑን በመግለጽ ይዞታውን  እንዲለቁ ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡……..

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

ጉዳዩ የእቁብ ገንዘብ ክፍያ የሚመለከት ነዉ፡፡ክርክሩ የተጀመረው በጋምቤላ ክልል ማጀንግ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ከሳሽ በመሆን  ተጠሪዎች ላይ ያቀረበው ክስ በ1ኛ ተጠሪ ሰብሳቢነት እና በ2ኛ ተጠሪ ፀኃፊነት በየሳምንቱ የሚጣል እና የሚወጣ የጥምር የሚባል የእቁብ ማህበር በ2007 ዓ.ም መተዳደሪያ ደንብ እና መዝገብ ያለው የአንድ እጣ ብር 3000 ሲሆን እኔም በድርሻዬ የአንድ እጣና ግማሽ ማለትም ብር 4500 በየሳምንቱ እየጣልኩኝ በወቅቱ በደረሰብኝ ድንገተኛ የግድያ ሙከራ ወንጀል ጉዳት ደርሶብኝ መናገርና መንቀሳቀስ ሳልችል ለተከታታይ አራት ዓመት ቆይቼ ሊደርሰኝ የሚገባኝን ብር 166,500 ተጠሪዎች ከሰበሰቡ በኋላ ያልሰጡኝ በመሆኑ ከህጋዊ ወለድ ጋር በአንድነት እንዲከፍሉኝ እንዲወሰን የሚል ሲሆን ተጠሪዎች በበኩላቸዉ አመልካች ሲከፍል የነበረው የአንድ ዕጣ መሆኑንና በደረሰበት አደጋ ምክንያት መናገር እና መፃፍ ባለመቻሉ የሚከፍለውን ሙሉ የአንድ ዕጣ በቀን 26/08/2007 ዓ.ም ያለ ዕጣ ዋስ በማስጠራት ዋስ አቶ ደረጀ ማዘንጊያ አማካይነት ብር 111,000 ተቀብሎ በዋሱ አማካይነት ሙሉ ዕቁቡን ገንዘብ በመክፈል ካጠናቀቀ በኋላ እስከ 2011 ዓ.ም ድረስ የዕቁቡ ማህበር አባል ሆኖ እያለ ያለአግባብ ለመበልፀግ ሲል ያቀረበው ክስ በመሆኑ ክሱ ውድቅ እንዲደረግልን በማለት ተከራክረዋል፡፡………..

እነ አቶ አየናዉ አላምረዉ ወ-ሮ መሰረት ሉሉ የሰ-መ-ቁ 183394

እነ አቶ አየናዉ አላምረዉ ወ-ሮ መሰረት ሉሉ የሰ-መ-ቁ 183394

ይህ የወጪና ኪሳራ፣ የተቋረጠ ገቢን የሚመለከት ክርክር የተጀመረዉ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሲሆን፣ የአሁን አመልካች የሥር ተከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር 1ኛ ከሳሽ፣ በዚህ ችሎት የክርክሩ ተካፋይ ያልሆነዉ መርጌታ ታዬ ሉሉ ሌሎች የሥር 2ኛ ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር። ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ.300510 በ02/11/2011 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ።

የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ በሥር ከሳሾች እና በሥር ተከሳሽ መካከል የነበረዉን የወጪና ኪሳራ እንዲሁም ከቤት ጋር በተያያዘ የተቋረጠ ገቢን የሚመለከት ክርክር የሥር የከፍተኛ ፍ/ቤት ግራ ቀኙን አከራክሮ ዉሳኔ ከሰጠ በኋላ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ.208 መሰረት የቀረበዉን አቤቱታ ተከትሎ ጉዳዩን ድጋሚ በማየት በመ.ቁ.61826 በ16/9/2010 ዓ.ም በሰጠዉ ዉሳኔ የሥር ተከሳሽ በክርክሩ ምክንያት በሥር ከሳሻ ላይ ለደረሰዉ ወጪና ኪሳራ ብር 210.00 [ሁለቶ አስር] እንዲከፍላት፤ የታጠዉን የቤት ኪራይ ገቢን በተመለከተ የተጠየቀዉ ዳኝነት የክስ ምክንያት ስለሌለዉ ዉድቅ ነዉ በማለት ወስኗል። የሥር 1ኛ ከሳሽ በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ያቀረበች ቢሆንም ፍ/ቤቱ ይግባኙን በትዕዛዝ ዉድቅ በማድረግ የሥር ፍ/ቤት ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል። የሥር ከሳሽ አሁንም በዚህ ትዕዛዝ ቅር በመሰኘት የሰበር አቤቱታ ለኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረበች ሲሆን ችሎቱም ግራ ቀኙን በማከራከር በሰጠዉ ዉሳኔ የሥር የከፍተኛዉ ፍ/ቤት የሥር ተከሳሽ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ.208 መሰረት ያቀረበዉን አቤቱታ ተቀብሎ የቀደመዉን ዉሳኔ በመሻር የሰጠዉ ዉሳኔ የሕግ ድጋፍ የለዉም በማለት በመሻር ወስኗል። የአሁን ሰበር አቤቱታ የቀረበዉ በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ለማስለወጥ ነዉ። የአሁን አመልካች ባቀረበዉ የሰበር አቤቱታ፡ ግራ ቀኙ አንድ ክልል ነዋሪዎች በመሆናችን የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይህን ጉዳይ ለማየት ስልጣን እንደሌለዉ የአሁን አመልካች ለክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ባቀረበዉ መልስ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አንሶቶ ነበር። የሥር የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤትም ሆነ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት የግራ ቀኙን ጉዳይ ያዩት በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 80 [2፣ 4] መሰረት በተሰጠዉ የዉክልና ስልጣን በሆኑ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት በሰጠዉ ዉሳኔ ቅሬታ መቅረብ ያለበት በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጽ 10 [1] መሰረት ለፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት ሆኖ ሳለ የሥር የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ይህን መቃወሚያ በዝምታ በማለፍ የሰጠዉ ዉሳኔ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ.244 [1] እና በዚህ ችሎት ከተሰጠዉ አስገዳጅ የህግ ትርጉም የሚቃረን ነዉ። ስለሆነም የሥር የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይህን ጉዳይ በሰበር አይቶ ለመወሰን ስልጣን ሳይኖረዉ የሰጠዉ ዉሳኔ ሕጋዊ መሰረት የሌለዉ ስለሆነ እንዲሻርልኝ በማለት በዝርዝር አመልክቷል።...........

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

ጉዳዩ የእቁብ ገንዘብ ክፍያ የሚመለከት ነዉ፡፡ክርክሩ የተጀመረው በጋምቤላ ክልል ማጀንግ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ከሳሽ በመሆን  ተጠሪዎች ላይ ያቀረበው ክስ በ1ኛ ተጠሪ ሰብሳቢነት እና በ2ኛ ተጠሪ ፀኃፊነት በየሳምንቱ የሚጣል እና የሚወጣ የጥምር የሚባል የእቁብ ማህበር በ2007 ዓ.ም መተዳደሪያ ደንብ እና መዝገብ ያለው የአንድ እጣ ብር 3000 ሲሆን እኔም በድርሻዬ የአንድ እጣና ግማሽ ማለትም ብር 4500 በየሳምንቱ እየጣልኩኝ በወቅቱ በደረሰብኝ ድንገተኛ የግድያ ሙከራ ወንጀል ጉዳት ደርሶብኝ መናገርና መንቀሳቀስ ሳልችል ለተከታታይ አራት ዓመት ቆይቼ ሊደርሰኝ የሚገባኝን ብር 166,500 ተጠሪዎች ከሰበሰቡ በኋላ ያልሰጡኝ በመሆኑ ከህጋዊ ወለድ ጋር በአንድነት እንዲከፍሉኝ እንዲወሰን የሚል ሲሆን ተጠሪዎች በበኩላቸዉ አመልካች ሲከፍል የነበረው የአንድ ዕጣ መሆኑንና በደረሰበት አደጋ ምክንያት መናገር እና መፃፍ ባለመቻሉ የሚከፍለውን ሙሉ የአንድ ዕጣ በቀን 26/08/2007 ዓ.ም ያለ ዕጣ ዋስ በማስጠራት ዋስ አቶ ደረጀ ማዘንጊያ አማካይነት ብር 111,000 ተቀብሎ በዋሱ አማካይነት ሙሉ ዕቁቡን ገንዘብ በመክፈል ካጠናቀቀ በኋላ እስከ 2011 ዓ.ም ድረስ የዕቁቡ ማህበር አባል ሆኖ እያለ ያለአግባብ ለመበልፀግ ሲል ያቀረበው ክስ በመሆኑ ክሱ ውድቅ እንዲደረግልን በማለት ተከራክረዋል፡፡………..

First145146147148150152153154Last