አቶ ግደይ ገ-ጻድቃን ገ-ማርያም እና ወ-ሮ ክንድሀፍቲ ኢታይ የሰ-መ-ቁ 179589

አቶ ግደይ ገ-ጻድቃን ገ-ማርያም እና ወ-ሮ ክንድሀፍቲ ኢታይ የሰ-መ-ቁ 179589

የሰበር አቤቱታው የቀረበው አመልካች የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ/ቁ 24172 በቀን 08/04/2011 ዓ/ም የሰጠው ትዕዛዝ እና የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ/ቁ 226191 በቀን 19/07/2011 ዓ/ም የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ይታረምልኝ በማለት ስለጠየቁ ነው፡፡ ክርክሩ የዕግድ ትዕዛዝ እንዲነሳ በአመልካች የቀረበን አቤቱታ የሚመለከት ነው፡፡በፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በከሳሽ ወ/ሮ ክንድሀፍቲ ኢታይ (የአሁን ተጠሪ) እና በተከሳሽ አቶ ፀጉ ብርሃነ መካከል በነበረው የባልና ሚስት የንብረት ክርክር ጉዳይ የአሁን ተጠሪ ንብረት እየሸሸ በመሆኑ ይታገድልኝ በማለት በፀጉ ብርሃነ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሚታወቁ መኪኖች ላይ የእርድ ትዕዛዝ አሰጥተዋል፡፡በፀጉ ብርሃነ ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እግዱ እንዲነሳ ጠይቆም በቅድሚያ ዋስትና እንዲያስይዝ ተጨማሪ ትዕዛዝ ተሰጥቶበታል፡፡…..

ወ-ሮ ተሚማ ሬድዋን በሽር እናአቶ በድሩ ሰማን፣አቶ ደሊል በድሩ የሰ-መ-ቁ 179231

ወ-ሮ ተሚማ ሬድዋን በሽር እናአቶ በድሩ ሰማን፣አቶ ደሊል በድሩ የሰ-መ-ቁ 179231

 ጉዳዩ የባልና ሚስት የጋራ ሀብት በሆነ ንብረት ላይ ይገባኛል የሚለው ሰው በአንደኛው ተጋቢ ላይ ብቻ ክስ አቅርቦ ተከሣሹም  ንብረቱ የከሣሽ ነው ሲል አምኖ መከራካሩን ተክተሎ በክሱ መሰረት ከተወሰነ በኋላ ሌላኛው ተጋቢ የመቃወም አቤቱታ ሲያቀርብ ብቻውን ተከሻስ የነበረው ተጋቢ  ቀደም ሲል ያቀረበውን ክርክር ሣይለውጥ በመቀጠሉ የተወሰነው የንብረቱ ክፍል የተጋቢዎች የጋራ ሃብት መሆኑ ቢረጋገጥም በክርክሩ ያመነው ተጋቢ ድርሻ ለከሣሽ ወገን እንዲተላለፍለት መወሰኑ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ነው ተብሎ እንዲታረም የቀረበን የሰበር አቤቱታ ይመለከታል፡፡……….

እነ ወ-ሮ ጀማነሽ ቀነኒ፣አቶ አሰፋ ሸቡ እና ወ-ሮ ብርቱካን ሸቡ የሰ-መ-ቁጥር 177205

እነ ወ-ሮ ጀማነሽ ቀነኒ፣አቶ አሰፋ ሸቡ እና ወ-ሮ ብርቱካን ሸቡ የሰ-መ-ቁጥር 177205

ለዚህ የሰበር መዝገብ ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ የቀረበው አመልካች ግንቦት 12 ቀን 2011 ዓ.ም በተፃፈ አቤቱታ የደቡብ ብ/ብ/ህ/መ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመ/ቁጥር 11920 የካቲት 12 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ እና የደቡብ ብ/ብ/ህ/መ. ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁጥር 12667 ግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልን በማለት ቅሬታቸውን በማቅረባቸው ነው፡፡ ቅሬታቸውም አቤት የተባለበትን ውሣኔ፣ አመልካቾች የሚቃወሙባቸውን ምክንያቶች የሚዘረዝርና በሰበር ሰሚው ችሎት በኩል ሊታይልን ይገባል የሚሉትን ዳኝነት የሚጠይቅ ሲሆን፣ የስር ፍ/ቤት የከተማ ማዘጋጃ ቤቱ አጣርቶ ገልጾ እያለ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ከቀበሌ ጠይቆ በዚሁ ተመስርቶ የሰጠው ውሳኔ ተገቢ አይደለም፡፡ የውርስ አጣሪው ከሳሽ 12,000 ብር የተቀበለች መሆኑን ጭምር ከሪፖርቱ ጋር ሰነዱን አቅርቦ እያለ እና ድርሻዋን መውሰዷ ተረጋግጦ እያለ በድካሚ ትካፈል ተብሎ መወሰኑ ተገቢ ባለመሆኑና የተጠሪ ክስም በይርጋ ውድቅ መሆን ስገባ መታለፉ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ይታረምልኝ የሚልነው፡፡..........

አቶ ረዲ አህመድ እና ወ-ሮ መኪያ ሀሰን የሰ-መ-ቁ 175719

አቶ ረዲ አህመድ እና ወ-ሮ መኪያ ሀሰን የሰ-መ-ቁ 175719

ይህ የባልና ሚስት የንብረት ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን፣ የአሁን አመልካች የሥር ከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር። ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ.ቁ.223910 በ10/8/2011 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ። የአሁን አመልካች በሥር ፍ/ቤት ባቀረቡት ክስ በአመልካች እና በተጠሪ መካከል የነበረዉ ጋብቻ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ሸሪዓ ፍ/ቤት በሰጠዉ ዉሳኔ ጋብቻችን በፍቺ እንዲፈርስ ወስኗል። ስለሆነም አመልካች እና ተጠሪ በጋራ የፈራነዉ በሱሉልታ ከተማ ልዩ ስሙ ድሬ ጀርባ የሚገኘዉ የቤት ቁጥር 632 SUL 2.1 የሆነዉ በተጠሪ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ የመኖሪያ ቤት እንዲንካፈል እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል። የአሁን ተጠሪ በዚህ ክስ ላይ ባቀረቡት መልስ ይህን ቤት ተጠሪ ከአመልካች ጋር የነበረን ጋብቻ ከተቋረጠ በኋላ ተጠሪ ከግለሰብ ገንዘብ ተበድሬ የተሰራ ስለሆነ የጋራ ንብረት ሳይሆን የግል ንብረቴ በመሆኑ ክሱ ተቀባይነት የለዉም በማለት ተከራክሯል።………

እነ ወ/ሮ አያልነሽ ፈንቴ እና ወ/ሮ ብርሃኔ ተካ የሰ-መ-ቁ182110

እነ ወ/ሮ አያልነሽ ፈንቴ እና ወ/ሮ ብርሃኔ ተካ የሰ-መ-ቁ182110

አመልካች ለዚህ ችሎት ሐምሌ 19 ቀን 2011 ዓ/ም ባቀረቡት አቤቱታ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 62378 መጋቢት 11 ቀን 2009 ዓ/ም በዋለው ችሎት ማስረጃ ሳይሰማ አመልካች የሟች ሚስት አይደሉም በማለት የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ አቅርበው ፍርድ ቤቱም በመዝገብ ቁጥር 194677 መጋቢት 11 ቀን 2009 ዓ/ም በዋለው ችሎት ያቀረቡትን አቤቱታ በመሰረዙ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ቅሬታ አቅርበው ችሎቱም በመዝገብ ቁጥር 148513 የሰበር አቤቱታቸውን የሰረዘው ሆኖ እያለ እና የአሁን ተጠሪ በሰበር መዝገብ ቁጥር 152523 ባቀረቡት ቅሬታ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በፊት የተሰጠን ውሳኔን ጠቅሶ ግራ ቀኙ የሟች ሚስቶች አይደሉም በማለት የሰጠውን ውሳኔ ሙሉ በሙሉ በመሻር በማስረጃ ተጣሪቶ እንዲወሰን ወደ ሥር ፍርድ ቤት መልሶት እያለ ፤ ይህ ውሳኔ ለአመልካችም ተፈፃሚነት ሊኖረው ሲገባ በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ስላላቀረብሽ ውሳኔውን እንደተቀበልሽ ይቆጠራል በማለት ከክርክሩ እንዲወጡ በማድረግ ተጠሪ ብቻ ሚስትነታቸውን እንዲያረጋግጡ መደረጉ የእኩልነት መርህን የሚጥስ ነው በማለት ብይኑ ተሽሮ ሚስት መሆናቸውን በማስረጃ ማረጋገጥ እንዲችሉ እንዲወሰንላቸው ጠይቋል።………….

First1516171820222324Last