Login
  • Register
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • Message from the President
    • History and Traditions
    • Vision Mission and Mandate
    • President
      • Current President
      • Former Presidents
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • Judges
      • Current
      • Former Judges
    • Judicial Administration Council
    • Court Administration & Directorates
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • E-Filing
    • Quick Start Guide
      • Registration
      • E-Filing
    • User Guide
    • Rules and Guidelines
    • Forms
    • Tutorials
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

ጉዳዩ የእቁብ ገንዘብ ክፍያ የሚመለከት ነዉ፡፡ክርክሩ የተጀመረው በጋምቤላ ክልል ማጀንግ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ከሳሽ በመሆን  ተጠሪዎች ላይ ያቀረበው ክስ በ1ኛ ተጠሪ ሰብሳቢነት እና በ2ኛ ተጠሪ ፀኃፊነት በየሳምንቱ የሚጣል እና የሚወጣ የጥምር የሚባል የእቁብ ማህበር በ2007 ዓ.ም መተዳደሪያ ደንብ እና መዝገብ ያለው የአንድ እጣ ብር 3000 ሲሆን እኔም በድርሻዬ የአንድ እጣና ግማሽ ማለትም ብር 4500 በየሳምንቱ እየጣልኩኝ በወቅቱ በደረሰብኝ ድንገተኛ የግድያ ሙከራ ወንጀል ጉዳት ደርሶብኝ መናገርና መንቀሳቀስ ሳልችል ለተከታታይ አራት ዓመት ቆይቼ ሊደርሰኝ የሚገባኝን ብር 166,500 ተጠሪዎች ከሰበሰቡ በኋላ ያልሰጡኝ በመሆኑ ከህጋዊ ወለድ ጋር በአንድነት እንዲከፍሉኝ እንዲወሰን የሚል ሲሆን ተጠሪዎች በበኩላቸዉ አመልካች ሲከፍል የነበረው የአንድ ዕጣ መሆኑንና በደረሰበት አደጋ ምክንያት መናገር እና መፃፍ ባለመቻሉ የሚከፍለውን ሙሉ የአንድ ዕጣ በቀን 26/08/2007 ዓ.ም ያለ ዕጣ ዋስ በማስጠራት ዋስ አቶ ደረጀ ማዘንጊያ አማካይነት ብር 111,000 ተቀብሎ በዋሱ አማካይነት ሙሉ ዕቁቡን ገንዘብ በመክፈል ካጠናቀቀ በኋላ እስከ 2011 ዓ.ም ድረስ የዕቁቡ ማህበር አባል ሆኖ እያለ ያለአግባብ ለመበልፀግ ሲል ያቀረበው ክስ በመሆኑ ክሱ ውድቅ እንዲደረግልን በማለት ተከራክረዋል፡፡………..

እነ አቶ አየናዉ አላምረዉ ወ-ሮ መሰረት ሉሉ የሰ-መ-ቁ 183394

እነ አቶ አየናዉ አላምረዉ ወ-ሮ መሰረት ሉሉ የሰ-መ-ቁ 183394

ይህ የወጪና ኪሳራ፣ የተቋረጠ ገቢን የሚመለከት ክርክር የተጀመረዉ በምስራቅ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሲሆን፣ የአሁን አመልካች የሥር ተከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር 1ኛ ከሳሽ፣ በዚህ ችሎት የክርክሩ ተካፋይ ያልሆነዉ መርጌታ ታዬ ሉሉ ሌሎች የሥር 2ኛ ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር። ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ.300510 በ02/11/2011 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ።

የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ በሥር ከሳሾች እና በሥር ተከሳሽ መካከል የነበረዉን የወጪና ኪሳራ እንዲሁም ከቤት ጋር በተያያዘ የተቋረጠ ገቢን የሚመለከት ክርክር የሥር የከፍተኛ ፍ/ቤት ግራ ቀኙን አከራክሮ ዉሳኔ ከሰጠ በኋላ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ.208 መሰረት የቀረበዉን አቤቱታ ተከትሎ ጉዳዩን ድጋሚ በማየት በመ.ቁ.61826 በ16/9/2010 ዓ.ም በሰጠዉ ዉሳኔ የሥር ተከሳሽ በክርክሩ ምክንያት በሥር ከሳሻ ላይ ለደረሰዉ ወጪና ኪሳራ ብር 210.00 [ሁለቶ አስር] እንዲከፍላት፤ የታጠዉን የቤት ኪራይ ገቢን በተመለከተ የተጠየቀዉ ዳኝነት የክስ ምክንያት ስለሌለዉ ዉድቅ ነዉ በማለት ወስኗል። የሥር 1ኛ ከሳሽ በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ይግባኝ ለኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ያቀረበች ቢሆንም ፍ/ቤቱ ይግባኙን በትዕዛዝ ዉድቅ በማድረግ የሥር ፍ/ቤት ዉሳኔ በማጽናት ወስኗል። የሥር ከሳሽ አሁንም በዚህ ትዕዛዝ ቅር በመሰኘት የሰበር አቤቱታ ለኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ያቀረበች ሲሆን ችሎቱም ግራ ቀኙን በማከራከር በሰጠዉ ዉሳኔ የሥር የከፍተኛዉ ፍ/ቤት የሥር ተከሳሽ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ.208 መሰረት ያቀረበዉን አቤቱታ ተቀብሎ የቀደመዉን ዉሳኔ በመሻር የሰጠዉ ዉሳኔ የሕግ ድጋፍ የለዉም በማለት በመሻር ወስኗል። የአሁን ሰበር አቤቱታ የቀረበዉ በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ለማስለወጥ ነዉ። የአሁን አመልካች ባቀረበዉ የሰበር አቤቱታ፡ ግራ ቀኙ አንድ ክልል ነዋሪዎች በመሆናችን የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይህን ጉዳይ ለማየት ስልጣን እንደሌለዉ የአሁን አመልካች ለክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ባቀረበዉ መልስ የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አንሶቶ ነበር። የሥር የክልሉ ከፍተኛ ፍ/ቤትም ሆነ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት የግራ ቀኙን ጉዳይ ያዩት በሕገ መንግስቱ አንቀጽ 80 [2፣ 4] መሰረት በተሰጠዉ የዉክልና ስልጣን በሆኑ፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት በሰጠዉ ዉሳኔ ቅሬታ መቅረብ ያለበት በአዋጅ ቁጥር 25/1988 አንቀጽ 10 [1] መሰረት ለፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት ሆኖ ሳለ የሥር የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት ይህን መቃወሚያ በዝምታ በማለፍ የሰጠዉ ዉሳኔ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ.244 [1] እና በዚህ ችሎት ከተሰጠዉ አስገዳጅ የህግ ትርጉም የሚቃረን ነዉ። ስለሆነም የሥር የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ይህን ጉዳይ በሰበር አይቶ ለመወሰን ስልጣን ሳይኖረዉ የሰጠዉ ዉሳኔ ሕጋዊ መሰረት የሌለዉ ስለሆነ እንዲሻርልኝ በማለት በዝርዝር አመልክቷል።...........

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

እነ አቶ ሳሙኤል ገዛኸኝ፣ አቶ መኩሪያ ታረቀኝ እና አቶ ፍሰሃ እርቅይሁን የሰ-መ-ቁ-191141

ጉዳዩ የእቁብ ገንዘብ ክፍያ የሚመለከት ነዉ፡፡ክርክሩ የተጀመረው በጋምቤላ ክልል ማጀንግ ብሄረሰብ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ከሳሽ በመሆን  ተጠሪዎች ላይ ያቀረበው ክስ በ1ኛ ተጠሪ ሰብሳቢነት እና በ2ኛ ተጠሪ ፀኃፊነት በየሳምንቱ የሚጣል እና የሚወጣ የጥምር የሚባል የእቁብ ማህበር በ2007 ዓ.ም መተዳደሪያ ደንብ እና መዝገብ ያለው የአንድ እጣ ብር 3000 ሲሆን እኔም በድርሻዬ የአንድ እጣና ግማሽ ማለትም ብር 4500 በየሳምንቱ እየጣልኩኝ በወቅቱ በደረሰብኝ ድንገተኛ የግድያ ሙከራ ወንጀል ጉዳት ደርሶብኝ መናገርና መንቀሳቀስ ሳልችል ለተከታታይ አራት ዓመት ቆይቼ ሊደርሰኝ የሚገባኝን ብር 166,500 ተጠሪዎች ከሰበሰቡ በኋላ ያልሰጡኝ በመሆኑ ከህጋዊ ወለድ ጋር በአንድነት እንዲከፍሉኝ እንዲወሰን የሚል ሲሆን ተጠሪዎች በበኩላቸዉ አመልካች ሲከፍል የነበረው የአንድ ዕጣ መሆኑንና በደረሰበት አደጋ ምክንያት መናገር እና መፃፍ ባለመቻሉ የሚከፍለውን ሙሉ የአንድ ዕጣ በቀን 26/08/2007 ዓ.ም ያለ ዕጣ ዋስ በማስጠራት ዋስ አቶ ደረጀ ማዘንጊያ አማካይነት ብር 111,000 ተቀብሎ በዋሱ አማካይነት ሙሉ ዕቁቡን ገንዘብ በመክፈል ካጠናቀቀ በኋላ እስከ 2011 ዓ.ም ድረስ የዕቁቡ ማህበር አባል ሆኖ እያለ ያለአግባብ ለመበልፀግ ሲል ያቀረበው ክስ በመሆኑ ክሱ ውድቅ እንዲደረግልን በማለት ተከራክረዋል፡፡………..

የእነ አምሳሉ አበራ እና አሻግሬ አበራ የሰ-መ-ቁ195361

የእነ አምሳሉ አበራ እና አሻግሬ አበራ የሰ-መ-ቁ195361

.   የእነ አምሳሉ አበራ  እና አሻግሬ አበራ የሰ-መ-ቁ195361 ጉዳዩ የገጠር መሬት ዉርስ ይመለከታል፡፡ክርክሩ የተጀመረው በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በእስቴ ወረዳ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ከሳሽ በመሆን በአሁኑ ተጠሪ ላይ ያቀረበው ክስ ሲሆን ይዘቱም በፍ/ቤቱ በመ/ቁ 0482874 በቀን 06/10/2010 ዓ/ም የሟች አያቶቼ አቶ አበረ ፋንቴ እና እማሆይ ፀሓይ ካሳ ወራሽነት አረጋግጨ እያለ ተጠሪም የልጅ ልጆች ሁነን እያለ የሟች መሬቶችን ብቻውን ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ በመያዝ አላካፍልም ስላለኝ የሟች አያቶቼን የይዞታ መሬት ድርሻዬን እንዲካፈለኝ ውሳኔ ይሰጥልኝ በማለት ዳኝነት የጠየቀ ሲሆን ተጠሪ የሰጠው መልስ ባጭሩ አመልካች የአያታችን መሬት መጠየቅ የሚችለው ወላጆቹ ሙተው ከሆነ ነው፤አባቱ እያለ ተተኪ ወራሽ ሊሆን ስለማይገባ እና የቤተሰብ አባል ያልሆነና በውርስ ላይም ያልጠየቀ እንዲሁም ሟች አቶ አበረ ፈንቴ የሞተዉ በ1995 ዓ.ም ስለሆነ አመልካች መብት የጠየቀዉ በ2010 ዓ.ም ስለሆነ ይህ ጊዜ ሲቆጠር 15 ዓመት በመሆኑ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1000(1) መሰረት በ3 ዓመት ይርጋ መብቱ ቀሪ ሆኗል በማለት የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ያቀረበ ሲሆን በአማራጭ አመልካች የቤተሰብ አባል አይደለም ከአያታቸው ጋር አላደገም በማለት ክሱ ዉድቅ እንዲደረግ መከራከሩን መዝገቡ ያሳያል፡፡……

እነ ሻለቃ ሰብሪ ቶፊቅ መሐመድ እና ሌ/ኮ/ል አለሙ ጌትነት አባተ የሰ-መ-ቁ 183941

እነ ሻለቃ ሰብሪ ቶፊቅ መሐመድ እና ሌ/ኮ/ል አለሙ ጌትነት አባተ የሰ-መ-ቁ 183941

የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጥር 16 ቀን 2011 በዋለው ችሎት በመዝገብ ቁጥር 72043 የሰጠው ፍርድ እና ውሳኔ እንዲሁም ይህን ፍርድ እና ውሳኔ በማፅናት የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰኔ 25 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት የሰጠው ፍርድ እና ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለት በሰበር እንድታረም አመልካች መስከረም 19 ቀን 2011 ዓ/ም ያቀረቡት የሰበር አቤቱታ ያስቀርባል ተብሎ መዝገቡ ለችሎት ቀርቧል። 

ጉዳዩ የተጀመረው በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች በ2ኛ ተከሳሽነት ፣ ተጠሪ በከሳሽነት፣ የኡዴ የጋራ የመኖሪያ ቤት ኃ/የተ/የሕ/ሥራ ማህበር በ1ኛ ተከሳሽነት ፣ የአቃ/ቃ/ክ/ከ/ንግድ እና ኢንደስትሪ ልማት ጽ/ቤት በ3ኛ ተከሳሽነት ተከራክረዋል፡፡ የሥር ከሳሽ በክሳቸው ፣ ቀደም ሲል የኢፌዴሪ አየር ሀይል ጠቅላይ መምሪያ አባል ሆነው ከሌሎች 11 የስራ ባልደረቦቻቸው ጋር በመሆን የሥር 1ኛ ተከሳሽ የሆነው የኡዴ የጋራ የመኖሪያ ቤት ኃ/የተ/የሕ/ሥራ ማህበር በ1997 ዓ/ም መስርተው የመዋጮ ገንዘብ በዝግ የባንክ ሂሳብ ቁጥር ገቢ አድርገው በአቃቂ ቃሊት ክፍለ ከተማ ወረዳ 02 ክልል ውስጥ ለቤት መስሪያ ቦታ በማህበሩ ስም ተረክበው ፤ ማህበሩ ቦታውን ተረክቦ ወደ ግንባታ ከመግባቱ በፊት ተጠሪ በ2001 ዓ/ም በወንጀል ተከሰው የዕድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸው በእስር ላይ እያሉ የቤቱን ጉዳይ እንዲከታተሉላቸው ወንድማቸው አቶ ቢንያም ጌትነትን ወክለው እያለ ፤ ተጠሪ ግዴታቸውን አልተወጡም በማለት የሥር 1ኛ ተከሳሽ ማስጠንቀቂያ ያወጣ ቢሆንም ተወካያቸው ማስጠንቀቂያው ተነስቶ ተጠሪ ግዴታቸውን ተወጥተው በአባልነታቸው እንዲቀጥሉ ያቀረቡትን ጥያቄ እና የሥር 3ኛ ተከሳሽ ድርጊቱ ተገቢ ስላልሆነ ቆሞ በአባልነታቸው እንዲቀጥሉ የጽፉትን ደብዳቤ ባለመቀበል ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያዎችን በመስጠት ተጠሪ ከአባልነት በማሰናበት አመልካችን መተካቱ ፤ የሥር 3ኛ ተከሳሽም መተካካቱ ተገቢ አለመሆኑን እያወቀ ከሥር 1ኛ ተከሳሽ ጋር ተባባሪ በመሆን በጋዜጣ በማውጣት ተጠሪ መብታቸውን እንዲያጡ ያደረገ በመሆኑ የሥር 1ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች አመልካችን ከማህበሩ አሰናብተው ተጠሪን ወደ አባልነት በመመለስ መብታቸውን እንዲያስከብሩላቸው ጠይቀዋል፡፡……

FirstPrevious23242526272829303132NextLast
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us 
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions