ወ-ሮ ትዕግስት ዓለሙ ቢ-አ-ኤ-ካ ኃ-የተ-የግል ማሕበ የጉባ ወረዳ አስተዳደር ጽ-ቤት፣የጉባ ወረዳ አካባቢ ጥበቃ፣መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ጽ-ቤት የሰ-መ-ቁ. 161449

ወ-ሮ ትዕግስት ዓለሙ ቢ-አ-ኤ-ካ ኃ-የተ-የግል ማሕበ የጉባ ወረዳ አስተዳደር ጽ-ቤት፣የጉባ ወረዳ አካባቢ ጥበቃ፣መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ጽ-ቤት የሰ-መ-ቁ. 161449

የሰበር አቤቱታው የቀረበው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት በሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው አመልካች በሥር ፍርድ ቤት ከሳሽ ሲሆኑ ተጠሪዎች ተከሳሾች ነበሩ፡፡ አመልካች ያቀረቡት ክስ በጉባ ወረዳ ማንኩሽ ቀበሌ 10 ሄክታር የእርሻ መሬት በ1987 ዓ/ም ተመርቼ በሕጋዊ መንገድ የያዝኩትን 1ኛ ተጠሪ ፈቃድ ሳያወጣ፣ 2ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎች ትክና ካሣ ሳይከፍሉኝ ያላግባብ የይዞታ መሬቴን ለ1ኛ ተጠሪ በ2008 ዓ/ም ስለሰጡብኝ የ2008/2009 ዓ/ም የምርት ዘመን ያጣሁት የሰሊጥ ምርት ብር 115,000.00፣ ማሳ ለማዘጋጀት ያወጣሁት ብር 40,000.00፣ የማፈናቀያ ካሣ ብር 115,000.00 እና 10 ሄክታር ትክ የእርሻ መሬት እንዲሰጡኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ ያቀረበው መልስ ካሣና ትክ አስተዳደሩ የሚሰጠው እንጂ 1ኛ ተጠሪን አይመለክትም፡፡ በኢንቨስትመንት በሕጋዊ ፈቃድ የተሰጠኝ ስለሆነ ልጠየቅ አይገባም ብሏል፡፡ 2ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎች በበኩላቸው መሬቱን የሠጠው የክልሉ ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ እንጂ እኛ አይደለንም፡፡ ካሣው የተጋነነ ነው፡፡ ብር 40,000.00 መሬቱን ለማጽዳት ስለመውጣቱ ማስረጃ አልቀረበም፡፡ ለ21 ዓመት መሬቱ ስለታረሰ የሚጸዳ ነገር የለውም፡፡ መሬቱን የሠጠው ቢሮ በክርክሩ ጣልቃ ገብቶ እንዲከራከር ይታዘዝልን ብለዋል፡፡ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃ፣ ማዕድንና ኢነርጂ ልማት ቢሮ  በክርክሩ ጣልቃ ገብቶ እንዲከራከር ታዞ ባለመቅረቡ ጉዳዩ በሌለበት ታይቷል፡፡..........

 

እነ ወ-ሮ ዘነበች ወንድሙ እና አቶ መስፍን ወንደሙ የሰ.መ.ቁ.185729

እነ ወ-ሮ ዘነበች ወንድሙ እና አቶ መስፍን ወንደሙ የሰ.መ.ቁ.185729

ይህ የዉርስ ንብረት ክርክር የተጀመረዉ በደቡብ ክልል ጊዲኦ ዞን በይርጋጨፌ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን፣ የአሁን አመልካቾች የሥር የመቃወም ተጠሪዎች፣ የአሁን ተጠሪ የሥር የመቃወም አመልካች ሆኖ ሲከራከሩ ነበር። ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ.75750 ጥቅምት 25 ቀን 2012 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልን በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ።………

እነ ወ-ሮ ጀማነሽ ቀነኒ፣አቶ አሰፋ ሸቡ እና ወ-ሮ ብርቱካን ሸቡ የሰ-መ-ቁጥር 177205

እነ ወ-ሮ ጀማነሽ ቀነኒ፣አቶ አሰፋ ሸቡ እና ወ-ሮ ብርቱካን ሸቡ የሰ-መ-ቁጥር 177205

ለዚህ የሰበር መዝገብ ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ የቀረበው አመልካች ግንቦት 12 ቀን 2011 ዓ.ም በተፃፈ አቤቱታ የደቡብ ብ/ብ/ህ/መ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመ/ቁጥር 11920 የካቲት 12 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ እና የደቡብ ብ/ብ/ህ/መ. ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁጥር 12667 ግንቦት 5 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ በሰበር ታይቶ እንዲታረምልን በማለት ቅሬታቸውን በማቅረባቸው ነው፡፡ ቅሬታቸውም አቤት የተባለበትን ውሣኔ፣ አመልካቾች የሚቃወሙባቸውን ምክንያቶች የሚዘረዝርና በሰበር ሰሚው ችሎት በኩል ሊታይልን ይገባል የሚሉትን ዳኝነት የሚጠይቅ ሲሆን፣ የስር ፍ/ቤት የከተማ ማዘጋጃ ቤቱ አጣርቶ ገልጾ እያለ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ከቀበሌ ጠይቆ በዚሁ ተመስርቶ የሰጠው ውሳኔ ተገቢ አይደለም፡፡ የውርስ አጣሪው ከሳሽ 12,000 ብር የተቀበለች መሆኑን ጭምር ከሪፖርቱ ጋር ሰነዱን አቅርቦ እያለ እና ድርሻዋን መውሰዷ ተረጋግጦ እያለ በድካሚ ትካፈል ተብሎ መወሰኑ ተገቢ ባለመሆኑና የተጠሪ ክስም በይርጋ ውድቅ መሆን ስገባ መታለፉ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ይታረምልኝ የሚልነው፡፡.........

አቶ ረዲ አህመድ እና ወ-ሮ መኪያ ሀሰን የሰ-መ-ቁ 175719

አቶ ረዲ አህመድ እና ወ-ሮ መኪያ ሀሰን የሰ-መ-ቁ 175719

ይህ የባልና ሚስት የንብረት ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን፣ የአሁን አመልካች የሥር ከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር። ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ.ቁ.223910 በ10/8/2011 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ። የአሁን አመልካች በሥር ፍ/ቤት ባቀረቡት ክስ በአመልካች እና በተጠሪ መካከል የነበረዉ ጋብቻ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ሸሪዓ ፍ/ቤት በሰጠዉ ዉሳኔ ጋብቻችን በፍቺ እንዲፈርስ ወስኗል። ስለሆነም አመልካች እና ተጠሪ በጋራ የፈራነዉ በሱሉልታ ከተማ ልዩ ስሙ ድሬ ጀርባ የሚገኘዉ የቤት ቁጥር 632 SUL 2.1 የሆነዉ በተጠሪ ስም ተመዝግቦ የሚገኝ የመኖሪያ ቤት እንዲንካፈል እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል። የአሁን ተጠሪ በዚህ ክስ ላይ ባቀረቡት መልስ ይህን ቤት ተጠሪ ከአመልካች ጋር የነበረን ጋብቻ ከተቋረጠ በኋላ ተጠሪ ከግለሰብ ገንዘብ ተበድሬ የተሰራ ስለሆነ የጋራ ንብረት ሳይሆን የግል ንብረቴ በመሆኑ ክሱ ተቀባይነት የለዉም በማለት ተከራክሯል።………

ዳግም አከበረኝ ከ ፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤሕግ

ዳግም አከበረኝ ከ ፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤሕግ

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ ቻለው አመልካች ሐምሌ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጽፎ ባቀረበው የሰበር አቤቱታ የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት በመ.ቁ 284716 ሠኔ 19 ቀን 2012 አመልካች የተከሰሰነት የወንጀል ሕግ ከ15 ዓመት እስከ 25 ዓመት ፅኑ እሥራት የሚያስቀጣ በመሆኑ በዋስ ቢወጣ ወንጀሉ ከሚያስከትለው ቅጣት ሙሉ በሙሉ እንደማይቀርብ ፍ/ቤቱ ግምት ስለወሰደ የዋስትና መብቱ ወንጀሉ ከሚያስከትለው ቅጣት ሙሉ በሙሉ እንደማይቀርብ ፍ/ቤቱ ግምት ስለወሰደ የዋስትና መብቱ በወ/መ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 67/ሀ መሠረት ተነፍጓል በማለት የሰጠው ትዕዛዝ፣ይህንኑ ትዕዛዝ በማፅናት የፌደራል ደፍተኛ ፍ/ቤት በመ.ቁ 255442 ሐምሌ 21 ቀን 2012 ዓ.ም ሰጠው ፍርድ መሠረታዊ የሆነ የሕግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ ሊታረም ገባል በማለት አቤቱታ በማቅረቡ ነው::

First2627282931333435Last