ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942 ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942 ይህ የስራ ስንብት ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁን አመልካች የሥር ከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር፡፡ ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ አመልካች የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ.ቁ.296508 በ29/10/2015 ዓ.ም የሰጠዉ ፍርድ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልን በማለት በማመልከቱ ነዉ፡፡ የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ የአሁን አመልካች በሥር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ባቀረበዉ የክስ አቤቱታ፡ አመልካች በተጠሪ ድርጅት በብሮ ስራ መሃንዲስ የሥራ መደብ ተቀጥሬ በወር 80,000 (ሰማንያ ሺህ) እየተከፈለኝ በአርሲ ሮቤ ዋቤ ሪቨር ፕሮጀክት ሲሰራ የቆየሁ ሲሆን ተጠሪ በ02/12/2014 ዓ.ም በሕገወጥ መንገድ ከሥራዬ ስላሰናበተኝ ተገቢ ክፍያዎችን እንዲከፍለኝ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡መለካም ንባብ….
እነ አቢብ አብዲ (3) ሰዎች እነ ዓሊ ዮሜ ዩሱፍ የሰ/መ/ቁጥር---250757 እነ አቢብ አብዲ (3) ሰዎች እነ ዓሊ ዮሜ ዩሱፍ የሰ/መ/ቁጥር---250757 ክስ ይዘት በአጭሩ: - ለ60 ዓመት በይዞታቸዉ ስር አድርገዉ ጫት በመትል፤ ቦቆሎና ማሽላ እየዘሩ ሲጠቀሙበት ነበረዉን በጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 20 ዉስጥ የሚገኘዉን ስፋቱ 60 ቆጢ የእርሻ መሬት ይዞታቸዉን በኃይል ወረራ በማድረግ አመልካቾች ይዘዉት በፀጥታ አስከባሪዎች እንዲያቆሙ ትዕዛዝ ቢሰጣቸዉም ከድርጊታቸዉ ሳይገቱየዘሩት እህል በከፊል አዉድመዋል፡፡ ስለሆነም አመልካቾች የፈጠሩት ሁከት እንዲወገድላቸዉ እንዲወሰን የሚጠይቅ ነዉ፡፡መልካም ንባብ….
ወ/ሮ አዳነች ሞኝነት እና አቶ ይልቃል አቤ የሰ.መ.ቁ 250332 ወ/ሮ አዳነች ሞኝነት እና አቶ ይልቃል አቤ የሰ.መ.ቁ 250332 ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነው ክርክር የተጀመረው በአማራ ክልል ባሶ ሊበን ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳው ፍርድ ቤት ተጠሪ ከሳሽ አመልካች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ በባሶ ሊበን ወረዳ ፍርድ ቤት ላይ ባቀረቡት ክስ አመልካች የተጠሪ አያት የሟች እማሆይ ጥሩ በላይ የቤተሰብ አባል ሳትሆንና ከሟቿ ጋር በአንድ ላይ ሆኖም ሆነ ከውጭ ሆኖ ሟቿን ሳትጦርና ሳትንከባከብ እንደጦረች እንደተንከባከበችና የሟቿ የቤተሰብ አባል እንደሆነች አስመስላ የሟቿን የእድሜ ባለፀጋነትን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ሟቿ ከቢሮ ሳይሄዱ እንደሄዱና በስጦታ እንዳስተላለፉላት በማድረግ ከመሬት ባለሙያ ጋር በመመሳጠር በ13/10/1998ዓ.ም የስጦታ ውል በማስሞላት የኑዛዜ ስጦታውን በመሬት አስተዳደር ጽ/ቤት በማስመዝገብ የኑዛዜ ስጦታ አለኝ በማለት አጭበርብራ ማስረጃ እንደያዘች” ገልጸው የመሬት ስጦታ ውሉም ሆነ ማስረጃው እንዲሰረዝላቸው ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….
እነ አቶ ግርማ አዳነ እና ላልይበላ ንግድ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሰ/መ/ቁጥር 247702 እነ አቶ ግርማ አዳነ እና ላልይበላ ንግድ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሰ/መ/ቁጥር 247702 የክሱ ይዘት በአጭሩ በላልይበላ ከተማ በንግድ ማህበር ተደራጅተን እየሰራን በሂደት 19 ክፍል የያዘ ሆቴል ገንብተን በለልይበላ ነጋዴዎች ማህበር ስም እየሰራን እያለ በአክሲዮን ሽያጭ ጠቅላላ ካፒታላችን ብር 2‚295‚500(ሁለት ሚሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና አምስት ሺ አምስት መቶ ብር) ስለደረሰ በ2002 ዓ.ም የማህበሩ ገንዘብ ያዥ የነበሩ የማህበሩ ስራ አስኪያጅ የሆነው ሁለተኛ ተከሳሽ የ10 ሰዎችን አክሲዮን ገዝቻለው በሚል ከ10 ሰዎች ውጪ ባለነው በ21 አባላት ስም እንደ አዲስ ማህበር መመስረት አለብን በማለት ለማህበሩ ሀሳብ አቅርቦ ከሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ የማህበሩ ስም ወደ ጌታቸው ግርማ እና ጓደኞቹ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በሚል ቀይሮ እየሰራ እያለ በማህበሩ አካላት መካከል አለመግባባት ተፈጥሮአል፡፡አመልካቾች እንደ ቁጥጥር ኮሚቴ አባልነታችን በመመስረቻ ፅሁፍ አንቀፅ 8 በተሰጠን ስልጣን መሰረት የአመራር ግድፈቶች እንዲስተካከሉ የምናደርገውን ቁጥጥር በመቃወም የመተዳደሪያ ደንቡ አንቀፅ 4(2) ባላገናዘበ መልኩ አለአግባብ ከማህበሩ ስላሰናበተን ወደ ማህበራችን እንድንመለስ፣ወደ ማህበሩ የማንመለስ ከሆነም ንብረቱ ተጣርቶ በአዲስ መልክ ከተመሰረተበት ከ1997 ጀምሮ ማህበሩ ኦዲት ተደርጎ ጉዳዩ የመጨረሻ ውሳኔ እስከሚሰጥበት የሚገኘው ድርሻችን እና ትርፋችን ታስቦ እንዲከፈለን የሚል ነው፡፡ተጠሪም በሰጡት መልስ በአመልካቾች የቀረበው ክስ በይርጋ ቀሪ ይሆናል የሚል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርበዋል፡፡ፍ/ቤቱም ይርጋን በተመለከተ የቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ በፍ/ህ/ቁጥር 448(2) መሰረት በጠቅላላ ጉባኤ ውሳኔ ላይ የሚቀርብ እንጂ ለማህበር ይፍረስልን እና ድርሻችን ይሰጠን ጥያቄ ላይ የሚቀርብ ስላልሆነ እንዲሁም ግንኙነታቸው በአንድ ጊዜ የሚጠናቀቅ ባለመሆኑ የይርጋውን መቃወሚያውን ውድቅ በማድረግ በፍሬ ነገሩ ላይ የግራ ቀኙን ማስረጃ መዝኖ የአመልካቾች ስንብት ህገ-ወጥ ስለሆነ ወደ ማህበሩ እንዲመለሱ እና ድርሻቸው ተካቶ የተሰራው የአክሲዮን ድልድል ታርሞ ክፍፍሉ ይፈፀም ሲል ወስኗል፡፡መልካም ንባብ….
እነ አቶ አበራ ነጋሽ ደምሴ(6) ሰዎች እና ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን፤ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ፅ/ቤት የሰበር መ/ቁ/245981 እነ አቶ አበራ ነጋሽ ደምሴ(6) ሰዎች እና ቦሌ ቡልቡላ ደብረ መድኃኔዓለም ቤ/ክርስቲያን፤ የቦሌ ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ፅ/ቤት የሰበር መ/ቁ/245981 ጉዳዩ የመሬት ባለይዞታነት መብት የሚመለከት ሲሆን በስር ፍርድ ቤት የአሁን አመልካቾች ከሳሽ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡አመልካቾች በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመ/ቁ131415 ባቀረቡት ክስ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 12 ክልል ውስጥ የሚገኝ ከ1-5 የተዘረዘሩት አመልካቾች ወላጅ አባት እና የ6ኛ አመልካች ወንድም የሆኑት በጋራ ይዘው ይጠቀሙበት የነበረ በግምት ከ60‚000 ካ.ሜ ያላነሰ ስፋት ያለው አዋሳኞቹ በክሱ የተጠቀሰ ይዞታ ለረጅም ጊዜ ግብር እየገበሩበት ሲጠቀሙ የቆዩ ቢሆንም ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በ1ኛ ተጠሪ ቤተክርስቲያን የሰበካ ጉባኤ ኮሚቴ አባላት አማካኝነት የሀይማኖት ተቋሙ በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን መፈራት እና መከበር በመጠቀም የአመልካቾችን ይዞታ ለመቃብር ቦታ በሚል ምክንያት በመውሰድ ከፋፍሎ እና ሼዶችን ገንብቶ ለጋራዥ እና ሌሎች የንግድ አገልግሎቶች ኪራይ ገቢ እየሰበሰበ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲሰራ በማድረግ በህገወጥ መንገድ ይዞት ይገኛል፡፡ስለሆነም ለ1ኛተጠሪ የተሰጠው የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ተሰርዞ ለአመልካቾች እንዲመለስ ሲሉ ዳኝነት መጠየቃቸዉን መዝገቡ ያሣያል፡፡መልካም ንባብ….