የየጉለሌ ክ/ከ/ወረዳ 2 የመ/ቤቶች ጽ/ቤት እና ወ/ሪት ፍቅርተ ከተማ ሰ.መ.ቁ 204992

የየጉለሌ ክ/ከ/ወረዳ 2 የመ/ቤቶች ጽ/ቤት እና ወ/ሪት ፍቅርተ ከተማ ሰ.መ.ቁ 204992

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች መጋቢት 22 ቀን 2ዐ13 ዓ.ም. በተፃፈ የሰበር አቤቱታው የሚያከራክረው የመንግሥት ቤትን አስመልክቶ የስር ፍ/ቤት ተጠሪ መብት አላት ብሎ መወሰኑ እና የበላይ ፍ/ቤቶችም የስር ፍ/ቤት በውሣኔው የፈፀመውን ስህተት ሳያርሙ ማለፋቸው  መሠረታዊ የሕግ ስሕተት  በመሆኑ በሰበር ታይቶ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረቡ ነው፡፡

ጉዳዩን በመጀመሪያ ደረጃ ላየው የአዲስ አበባ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ተጠሪ አቅርባው የነበረው ክስ ከሚያከራክረው ቤት ተከራይ ከነበሩት አቶ አስፋው ቢራቱ ጋር በቤት ቁጥር 167 ውስጥ እንደልጅ ማደጓን፣ በቤቱ ውስጥ ያደገችው ከህፃንነቷ ጀምሮ መሆኑን እና እናቷም በህይወት የሌለች መሆኑን፣ ነገር ግን አመልካች ከቤቱ በህገወጥ መንገድ ስላስወጣት በቤቱ የመኖር መብት አላት ተብሎ እንዲወሰንላት ዳኝነት ጠይቃለች፡፡………

 

በደሴ ከተማ የሆጤ ክፍለ ከተማ አስተዳደር እና የወ/ሮ ማሚቴ ሁሴን ወራሾች እነ አያል አብርሃ የሰ/መ/ቁ፡-204074

በደሴ ከተማ የሆጤ ክፍለ ከተማ አስተዳደር እና የወ/ሮ ማሚቴ ሁሴን ወራሾች እነ አያል አብርሃ የሰ/መ/ቁ፡-204074

ክርክሩ የመንግስት የንግድ ቤትን የሚመለከት ሲሆን ጉዳዩ በተጀመረበት የደሴ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ፣ አመልካች ተከሳሽ እንዲሁም 2ኛ ተጠሪ ጣልቃ ገብ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ክርክሩ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡…………

ኦዲት ሰርቪስ ኮርፖሬሽን እና ፀጋ ረታ አስመጪ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር የሰ/መ/ቁ፡-197008

ኦዲት ሰርቪስ ኮርፖሬሽን እና ፀጋ ረታ አስመጪ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር የሰ/መ/ቁ፡-197008

ክርክሩ የሽያጭ ውልን መነሻ ያደረገ ሲሆን ጉዳዩ በተጀመረበት የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ አመልካች የካቲት 4 ቀን 2011 ዓ.ም ባቀረበው ክስ አመልካች የኮምፒዩተር እቃዎችን ለመግዛት ባወጣው ጨረታ ተጠሪ አሸንፎ እቃዎቹን አቅርቦ ክፍያ የተቀበለ ቢሆንም እቃዎቹን ከሰርቨሩ ጋር የሚያገናኙ ኬብሎችን ባለማቅረቡ ምክንያት እቃዎቹ የተፈለገውን አገልግሎት መስጠት አልቻሉም፡፡በመሆኑም ኬብሎቹን እንዲያቀርብ ወይም በወቅቱ የገበያ ዋጋ የእቃዎቹን ግምት ብር 182,900 ወጪና ኪሳራን ጨምሮ እንዲከፍል ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡ተጠሪ የካቲት 29 ቀን 2011 ዓ.ም በተፃፈ መልስ አመልካች እቃዎቹ ጉድለት ያለባቸው መሆኑን ካወቀበት ጊዜ ጀምሮ በ1 አመት ውስጥ ክስ ስላላቀረበ ክሱ በይርጋ ቀሪ ሆኗል የሚል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርቧል እንደሚከተለው ቀርቧል…………

ሕዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር እና እነ አቶ ታምሩ ደብሩ ሰ/መ/ቁ፡-191430

ሕዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር እና እነ አቶ ታምሩ ደብሩ ሰ/መ/ቁ፡-191430

ክርክሩ የአክሲዮን ድርሻ ትርፍ እንዲከፈል የቀረበ ክስን መሰረት ያደረገ ሲሆን ጉዳዩ በተጀመረበት የምእራብ ሐረርጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽና 1ኛ የከሳሽ ተከሳሽ፣ አመልካች ተከሳሽና የተከሳሽ ከሳሽ እንዲሁም 2ኛ ተጠሪ 2ኛ የተከሳሽ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡

1ኛ ተጠሪ ጥቅምት 23 ቀን 2009 ዓ.ም ፅፎ ባቀረበው ክስ በአመልካች ኩባንያ ውስጥ በልዩ ቁጥር 1457 የተመዘገበ የአክሲዮን ድርሻ ያለኝ ሲሆን በዓመቱ መጨረሻ ሒሳብ ተሰርቶ ሊከፈለኝ ሲገባ ከ2006 እስከ 2008 ያልተከፈለኝ የአክሲዮን ትርፍን ፍርድ ቤቱ ሂሳቡን በማስመርመር በግምት ብር 30,000 እንዲከፈለኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡…….   

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ-ክርስቲያን ኮሚሽን እና አቶ መስፍን አዱኛ የሰ/መ/ቁ. 211260

የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ-ክርስቲያን ኮሚሽን እና አቶ መስፍን አዱኛ የሰ/መ/ቁ. 211260

ጉዳዩ የግል የስራ ቅጥር ዉልን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በጀመረበት በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪ በቀን 30/06/2013 ዓ.ም ጽፎ ባቀረበው ክስ በአመልካች ድርጅት ውስጥ ከጥር 23 ቀን 2000 ዓ.ም ጀምሮ በፕሮጀክት ኦፊሰርነት በወር ብር 10,095.00 እየተከፈለኝ ሳገለግል የቆየሁ ቢሆንም አመልካች ምንም አይነት ማስጠንቀቂያ ሳይሰጠኝ፣ በማላውቀው እና በቂ ባልሆነ ምክንያት ጥቅምት 20 ቀን 2013 ዓ.ም የስራ ውሌን ያቋረጠው በመሆኑ ስንብቱ ህገ-ወጥ ነው ተብሎ ወደ ስራዬ እንድመለስ፤ ወደ ስራ የማልመለስ ከሆነ ደግሞ ያልተጠቀምኩበት የ58 ቀን የዓመት እረፍት ወደ ገንዘብ ተቀይሮ፣ ካሳ፣ የሶስት ወር የማስጠንቀቂያ ጊዜ ክፍያ፣ ክፍያ ለዘገየበት የሶስት ወር ደመወዝ ቅጣት እንዲከፍል እና የስራ ልምድ እንዲሰጠኝ ይወሰንልኝ በማለት የጠየቀዉን ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ እንደሚከተለው ቀርቧል…………

123468910Last