ወ/ሮ ሳፊያ ከድር እና እነ ሐጂ አማን ሐጂ ሁሴን (6ሰዎች) የሠ/መ/ቁጥር 254696

ወ/ሮ ሳፊያ ከድር እና እነ ሐጂ አማን ሐጂ ሁሴን (6ሰዎች) የሠ/መ/ቁጥር 254696

ጉዳዩ የውርስ ድርሻን የሚመለከት ሲሆን ክሱ በቀረበበት ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሰት ባሌ ዞን በርበሬ ወረዳ ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ 1ኛ ተጠሪ ተከሳሽ፤ ከ2ኛ እስከ 6ኛ ያሉ ተጠሪዎች ደግሞ ጣልቃ ገብ ተከራካሪዎች ነበሩ፡፡ አመልካች ያቀረቡት ክስ ይዘት፡- የ1ኛ ተጠሪ ሚስት የነበሩት እናታቸው ወ/ሮ ነኢማ ሀሚድ በሞት ከዚህ ዓለም መለየታቸውንና የሟች ወራሾች 7(ሰባት) እንደሆኑ ፤ ሟች ከ1ኛ ተጠሪ ጋር አፍርተዋል የሚሉትን መገኛቸው እና አዋሳኞቹ በክሱ ላይ ከተመለከቱት ከተራ ቁጥር 1-10 ከተዘረዘሩ ንብረቶች የሟች 50% የሚስት ድርሻ መሆኑን በመግለጽ 1ኛ ተጠሪ የውርስ ድርሻቸውን እንዲያክፈሏቸው እንዲወሰንላቸው ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…..

ወ/ሮ ኢየሩሳሌም ኃይሉ እና እነ ወ/ሮ እታገኘው ኃይሉ(4ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር 253718

ወ/ሮ ኢየሩሳሌም ኃይሉ እና እነ ወ/ሮ እታገኘው ኃይሉ(4ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር 253718

ጉዳዩ የውርስ ማጣራትን ተከትሎ የውርስ ሀብት ስለመሆኑ በተለየ ንብረት ላይ መብት ያላቸው ወራሾች ሊያገኙ ይችሉ የነበረውን ገቢ ቤቱን ከያዘው ሰው ለመጠየቅ ያላቸውን መብት የሚመለከት ነው፡፡ክርክሩ የተጀመረው በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን 1ኛ፣2ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎች ከሳሾች፣4ኛተጠሪ ጣልቃገብ አንደዚሁም አመልካች ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡በተጠሪዎች የቀረበው ክስ በአጭሩ ሟቾች አቶ ሀይሉ ደነቀው እና ወ/ሮ ልንገርሽ ይሁኔ በ422 ካ.ሜ ላይ ያረፈና የቤት ቁጥር 191 የሆነ ዋና ቤትና ሰርቪስ ቤቶች የነበሯቸው ሲሆን በመ/ቁ 82464 በፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት መናገሻ ምድብ ችሎት በነበረን የውርስ ሀብት ይጣራልን ክርክር ላይ የሟች አቶ ኃይሉ ደነቀው የውርስ ሀብት ተጣርቶ ውሳኔ ተሰጥቷል፡፡አመልካች በኑዛዜ የተላለፈላቸው 02 ክፍል ቤት ብቻ ሲሆን ክፍሎቹን እያከራዩ የሚጠቀሙበት ሆኖ በውርስ የሚደርሰንን ዋና ቤትና ሰርቪስ ቤቶችን ከህግ አግባብ ውጪ በመያዝ በዋናው ቤት እየኖሩበት አከራይተን እንዳንጠቀም በማድረግ ሰርቪስ ቤቶቹን ከተከራዩት ሰዎች ላይ የኪራዩን ገንዘብ በመሰብሰብ ለራሳቸው ጥቅም በማዋል ልናገኝ የሚገባውን ጥቅም አሳጥተውናል፡፡በመሆኑም በውሳኔው መሰረት የሚኖሩበትን ዋናውን ባለ ሶስት ክፍሉን ቤት እና የምያከራዩትን 03 ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ከነቦታው ለቀው እንዲያስረክቡን በተደጋጋሚ ከመጠየቅ ባሻገር ጥቅምት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ደግሞ የጹሑፍ ማስጠንቀቂያ የሰጠናቸው ቢሆንም አመልካች ቤቶቹን ለማስረከብ እንደዚሁም የቤቶቹ ኪራይ ገንዘብ ለመክፈል ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሟች ከሞቱበት ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ዋናው ቤት ቢከራይ በወር ብር 8000 (ስምንት ሺህ) ክስ እስካቀረብንበት ጊዜ ድረሰ ያለውን የ28 ወር ብር 224,000.00 (ሁለት መቶ ሀያ አራት ሺህ) እንዲከፍሉን፣የሚከራዩ 3 (ሶስት) ክፍል ሰርቪስ ቤቶች ሟች ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ እስከ ሚያዚያ ወር ብር 1500 (አንድ ሺ አምስት መቶ) ይከራይ የነበረው አመልካች ብር 300 (ሶስት መቶ) በመጨመር ብር 1800 (አንድ ሺ ስምንት መቶ)፣ ሌላው 1 (አንድ) ክፍል ቤት 500 (አምስት መቶ) ይከራይ ነበረው ብር 700 (ሰባት መቶ) እና ቀሪውን 01 ክፍል ቤት በብር 1000 (አንድ ሺህ) ልዩነቱ የ4 (አራት) ወር ብር 4000 (አራት ሺ)  ሟች ከሞቱበት ጊዜ ጀምሮ እስከ መጋቢት ወር መጨረሻ ክስ እስካቀረብንበት ጊዜ ድረስ ያለው ሲሰላ ሁለት ዓመት 24 (ሀያ አራት) ወር በመሆኑ ብር 70,000.00 (ሰባ ሺህ) በድምሩ ብር 74,000 (ሰባ አራት ሺህ) ልናገኝ የሚገባውን ጥቅም ያሳጡን ስለሆነ ዋናውን ቤት እና የሰርቪስ ቤቶቹን የኪራይ ገንዘብ ተከፍሎ እስከሚጠናቀቅበት ድረስ ከነወለዱ ታስቦ እንድከፍሉን እንዲወሰንልን የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…..

ሐረማያ ዩንቨርስቲ እና መላ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግል ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 253530

ሐረማያ ዩንቨርስቲ እና መላ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግል ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 253530

ጉዳዩ ከግንባታ ውል ጋር በተያያዘ በስር ፍ/ቤት የተሰጠው ውሳኔ በቀረበው የዳኝነት ጥያቄ መሰረት መሆን አለመሆኑን የሚመለከት ነው፡፡ የሰበርአቤቱታው የቀረበው የፌደራል ጠቅላይፍርድ ቤት በሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው በሥር ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ ሲሆን ተጠሪ ተከሳሽ ነበር፡፡አመልካች በ20/01/2013 ዓ/ም ጽፎ ባቀረበው ክስ አመልካች እና ተጠሪ በነሀሴ 2009ዓ/ም እ.ኤ.አ የማስፋፊያ ግንባታ ለማከናወን ተስማምተው ተጠሪ ሳይቱን በመረከብ የግንባታ ማስፋፊያ ስራውን ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በውሉ በተቀመጠው ጊዜ እና ጥራት የግንባታ ስራውን ማከናወን ባለመቻሉ በተደጋጋሚ ማስጠንቀቅያ ሰጥቶ ስራው 93% ላይ እያለ አመልካች ውሉን አቋርጧል፡፡ በመሆኑም ለአምስት ሕንፃዎች/ብሎኮች የስራ ግድፈት ማስተካከያ ብር 2,031,357.91፣ ለኩሽና፣ መጽሀፍት ቤትና ምግብ ቤት ማስተካከያ ሥራ ብር 350,759.30፣ የውሉ አፈጻጸም በመዝግየቱ በውሉ አንቀጽ 49.1 መሰረት የጠቅላላ ውሉን ዋጋ 10% የደረሰ ኪሣራ ብር 5,219,807.91እና የቀሪ ሥራ ማጠናቀቂያ ብር 492,255.18በድምሩ ብር 10,107,964.5 ተጠሪ እንዲከፍል እንዲወሰንለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ…..

አቶ ቴዎድሮስ መስፋን ህንፃ ሥራ ተቋራጭእና አዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት (በአሁኑ - የአ/አ ቤ/ልማት ኮርፖሬሽን) የሰበር መ/ቁ 253303

አቶ ቴዎድሮስ መስፋን ህንፃ ሥራ ተቋራጭእና አዲስ አበባ ቤቶች ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት (በአሁኑ - የአ/አ ቤ/ልማት ኮርፖሬሽን) የሰበር መ/ቁ 253303

በዚህ መዝገብ የተያዘው ጉዳይ የግንባታ ዉልን የሚመለከት ነዉ፡፡ ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ አመልካች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 04664 እና መ/ቁ 06910 አጣምሮ ሰኔ 24 ቀን 2014 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ ፤ የአዲስ አበባ ከተማ ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 37544 ህዳር 28 ቀን 2015 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ ፤ እንዲሁም የአዲስ አበባ ከተማ ሰበር ሰሚ ችሎት በመዝገብ ቁጥር 40218 ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ/ም የሰጠዉን ዉሳኔ በመቃወም ነው፡፡

ተጠሪ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ባቀረበው ክስ  ከአመልካች ጋር መስከረም 26 ቀን 2008 ዓ/ም ጠቅላላ ዋጋዉ የብር 19,044,907.52 (አስራ ዘጠኝ ሚሊዮን አርባ አራት ሺ ዘጠኝ መቶ ስባት ከ52/100) የህንፃ ግንባታ ዉል የፈፀምን ሲሆን መንግስት ለዜጎች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ በዘርፉ የሚገኙ ተቋራጮች በአንድ ዘርፍ ብቻ እንዲሳተፉ ስለተደረገ አመልካች በአዲስ አበባ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ሥር በግንባታ ስራ ያለመሳተፍ ማስረጃ አንዲያቀርብ ተጠይቆ ተጠሪ መስከረም 12 ቀን 2008 ዓ/ም የተፃፈ ሀሰተኛ ማስረጃ በማቅረቡ በዉሉ አንቀፅ 2 መሰረት የማጭበርበር ስራ የፈፀመ በመሆኑ ዉሉ የተቋረጠ ሲሆን አመልካች አለአግባብ የወሰደውን ብር 3,264,297.15 (ሶስት ሚሊዮን ሁለት መቶ ስልሳ አራት ሺ ሁለት መቶ ዘጠና ስባት ከ15/100) ቅድመ ክፍያ ለመመለስ ፍቃደኛ ስላልሆነ ይህን ገንዘብ ከወለድ ጋር እንዲከፍል ይወሰንልኝ በማለት ክስ አቅርቧል፡፡መልካም ንባብ…..

ደጀኔ ደበላ አልቀረበም እና ኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 251700

ደጀኔ ደበላ አልቀረበም እና ኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቢ ህግ የሰ/መ/ቁጥር 251700

ጉዳዩ ይለፍ ወረቀት ሳይይዙ የግብርና ምርቶችን ማጓጓዝ ወንጀል የሚመለከት ነው፡፡ክርክሩ የተጀመረው በሰሜን ሸዋ ዞን ወራ ጃርሶ ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ አመልካች ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡በተጠሪ የቀረበውም ክስ አመልካች የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ያወጣውን የገበያ ቁጥጥርና የምርት ጥራት አዋጅ ቁጥር 234/2013 አንቀፅ 26(3) እና 5 በመተላለፍ ታህሳስ 03 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ በግምት 4፡00 ሰአት በወራ ጃርሶ ወረዳ ቀሬ ጎሃ ከተማ ቀበሌ 02 ልዩ ቦታው ኬላ ተብሎ በሚጠራዉ ቦታ የሰሌዳ ቁጥር 3-16932 ኢት በሆነ ሲኖ ትራክ ተሽከርካሪ ላይ 220(ሁለት መቶ ሃያ) ኩንታል ባቄላ ግምቱ 836,000 (ስምንት መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ) የሆነውን ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል አቅጣጫ በመጓዝ ላይ እያለ ከላይ በተጠቀሰው ቦታ ሲደርስ በኬላ ተቆጣጣሪዎች ሲፈተሽ የንግድ ፍቃዱና የመነሻ እና መድረሻ የይለፍ ወረቀት ሳይይዝ በመጓዙ ያለ ፍቃድ የግብር ምርቶችን በማጓጓዝ ወንጀል ተከሷል የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…..

123468910Last