ፋል ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ እና አቶ አለማየሁ ገረመው የሰበር መ/ቁ/220193 ፋል ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ እና አቶ አለማየሁ ገረመው የሰበር መ/ቁ/220193 ጉዳዩ የአሰሪና ሰራተኛ የስራ ግንኙነት የሚመለከት ነዉ፡፡ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ ተጠሪ ከሳሽ በመሆን በአሁኑ አመልካች ላይ ባቀረበው ክስ በአመልካች ድርጅት ውስጥ ከህዳር 03/2011 ዓ.ም ጀምሮ በከባድ መኪና ሹፌርነት የስራ መደብ በወር ብር 4000 እየተከፈለኝ ሲሰራ ቆይቼ በስራ ላይ እያለሁ በደረሰዉ አደጋ ምክንያት ለተጎዳዉ ንብረትት እንደ ጥፋተኛ በመቁጠር በህገ-ወጥ መንገድ ከስራ ያሰናበተኝ በመሆኑ ስንብቱ ህገወጥ ነዉ ተብሎ ከህገወጥ የስራ ስንብት ጋር የተያያዙ ክፍያዎች እንዲከፈለኝ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡አመልካች በበኩሉ በሰጠው መልስ ተጠሪ ከስራ የተሰናበተው በከባድ ቸልተኝነት በፍጥነት በማሽከርከር ላይ ሳለ ከመስመር ወጥቶ በመገልበጥ አደጋ በማድረሱ በትራፊክ ሪፖርት እና በተያዘው ቃል ጉባኤ መሰረት በአዋጅ 1156/2011 አንቀጽ 27(ሸ) መሰረት በጥፋቱ የተሰናበተ በመሆኑ ስንብቱ ህጋዊ ነው፣ ስለዚህ የሚከፈለው ክፍያ የለም በማለት መከራከሩን መዝገቡ ያሣያል፡፡መልካም ንባብ…….
አቶ ዮናስ ሃይለ ብርሃን እና ወ/ሮ ቤተልሄም በርሄ ደስታ የሰ.መ.ቁ 219964 አቶ ዮናስ ሃይለ ብርሃን እና ወ/ሮ ቤተልሄም በርሄ ደስታ የሰ.መ.ቁ 219964 የጉዳዩ አመጣጥ ተጠሪ ከአመልካች ጋር የነበራቸው ጋብቻ በ25/4/11ዓ.ም በፍቺ ውሳኔ መፍረሱን ተከትሎ በአመልካች ላይ ባቀረቡት የተሻሻለ የንብረት ክፍፍል ክስ የግል ንብረቴ የሆኑት ከሟች አባቴ ኮሎኔል መከተ አወቀ ያገኘሁት የውርስ ሀብት ብር 723,447.39 ሲሆን ይህንን ገንዘብ ተጠሪ ለአመልካች በአደራ መልክ ብር 465,075.18 በአመልካች ስም በህብረት ባንክ በሂሳብ ቁጥር 14018161601533010 እ.ኤ.አ በ19/7/2015 ገቢ ያደረኩ ሲሆን በተጨማሪም እኤአ በ10/12/2015 በተጠሪ ስም ተመዝግቦ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወጪ አድርጌ ለአመልካች በአደራ መልክ ብር 228,200.00 የሰጠሁ ሲሆን ይህን ገንዘብ በውርስ ያገኘሁት በመሆኑ አመልካች እንዲመልስልኝ፤ የተጠሪ አይነታቸው እና ዋጋቸው የተገለጹ የወርቅ እና የብር ጌጣጌጦች በ24/12/10ዓ.ም አመልካች ስለወሰደብኝ እንዲመልስልኝ እንዲሁም ወጪ፤ ሰነዶች እና እቃዎች(ዝርዝራቸው የተገለጸ) አመልካች እንዲመልስልኝ፤ የንግድ ፈቃድ እንዲዘጋ፡፡በሚል ጠይቀዋል መልካም ንባብ…..
ቄስ ቀፀላጊዮርጊስ ደስታ እና አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር ፅ/ቤት ፤አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ቤቶች አስተዳደር የሰ/መ/ቁጥር 218309 ቄስ ቀፀላጊዮርጊስ ደስታ እና አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 03 አስተዳደር ፅ/ቤት ፤አዲስ ከተማ ክ/ከተማ ቤቶች አስተዳደር የሰ/መ/ቁጥር 218309 በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በከተማው የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በተጀመረው የሁከት ክርክር የሰበር አመልካች ከሣሽ፣ የሰበር አንደኛ ተጠሪ ተከሣሽ፣የሰበር ሁለተኛ ተጠሪ ጣልቃ ገብ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ አመልካች ግንቦት 2ቀን 2013ዓ/ም በተፃፈ ክሣቸው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 የቤት ቁጥር 648 የሚታወቀው ቤት የግል ቤታቸው መሆኑን፤ የቤት ቁጥር 649 ደግሞ የአስተዳደሩ ሆኖ አመልካች የግል ቤታቸው ስለጠበባቸው በኪራይ እንዲሰጣቸው ሕዳር 21ቀን 1985 ዓ/ም ጠይቀው በቃለ-ጉባኤ ተሰጥቷቸው እንዲሁም ቤቱ ወንዝ ዳር በመሆኑ በወንዙ የተወሰደውን የቤቱን ክፍል በራሣቸው ወጪ አድሰው ኪራይ እየከፈሉ በይዞታቸው አድርገው እስካሁን እየተጠቀሙበት መሆኑንና ውል እንዲይዝላቸው ኪራይም እንዲቀበላቸው ሲጠይቁት ይጠብቁ ሲላቸው ከቆየ በኋላ ሚያዚያ 28ቀን 2013ዓ/ም የግል ቤታቸውን ጨምሮ ማሸጉን ዘርዝረው የፈጠረባቸው ሁከት እንዲቆም የቤቱንም ኪራይ እንዲቀበል እንዲወሰንላቸው ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ………
አቶ ቴውድሮስ ፀጋዬ እና አቶ ሽመልስ አባተ የሰ/መ/ቁጥር 218235 አቶ ቴውድሮስ ፀጋዬ እና አቶ ሽመልስ አባተ የሰ/መ/ቁጥር 218235 በግራ ቀኙ መሃል በስር ፍርድ ቤት የነበረው ክርክር አመልካች በተጠሪ የተፈጠረው ሁከት እንዲወገድ ይወሰንልኝ በማለት አሻሽለው ያቀረቡትን ክስ መነሻ ያደረገ ሲሆን ተጠሪ ለዚህ ለተሻሻለ ክስ መልሳቸውን በሰጡበት እለት በተዘጋጀ አቤቱታ አመልካች ያቀረቡትን ክስ የሚረቱበት ህጋዊ ምክንያት የሌለ መሆኑን፤አመልካች በክሱ ቢረቱ በመሸጥ ወይም በመለወጥ በፍርድ ቤቱ የሚወሰነውን የክርክር ኪሳራና ካሳ የሚከፍሉበት የሚንቀሳቀስም ሆነ የማይንቀሳቀስ ንብረት የሌላቸው መሆኑን ገልፀው በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.200 መሰረት ዋስትና ብር 200,000.00 በሞዴል 85 እንዲያሲዙላቸው የጠየቁ ሲሆን፤አመልካች በሰጡት መልስም በክርክሩ ማን ይረታል የሚለው ማስረጃ ተመርምሮ ውሳኔ ሲሰጥ የሚታወቅ እንጂ ከወዲሁ የሚተነበይ አለመሆኑን፤ተጠሪ አቤቱታውን ያቀረቡት ክርክሩን ለማሰናከል የሕገ መንግስቱን አንቀፅ 37 በመተላለፍ መሆኑን ገልፀው አቤቱታው ውድቅ ሊደረግ ይገባል በማለት ተከራክረዋል፡፡መልካም ንባብ…….
ወ/ሮ ፍርኑስ ፈንቴ የደብረማዊ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት ሰ.መ.ቁ 217195 ወ/ሮ ፍርኑስ ፈንቴ የደብረማዊ ንዑስ ማዘጋጃ ቤት ሰ.መ.ቁ 217195 ጉዳየ የሥረ-ነገር ስልጣን ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው የአሁን አመልካች በቀን ሕዳር 18 ቀን 2013 ዓ.ም በተጻፈ የክስ አቤቱታ በይልማና ዴንሳ ወረዳ ፍ/ቤት በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ የነበራቸውን መሬት ለአመልካችና ለልጆቻቸው የቤት መስሪያ ቦታ ሳይሰጥና በቀሪው ይዞታ ላይ ካሳ ሳይከፈላቸው ተጠሪ ይዞታውን ለሌሎች ግለሰቦች የሰጠባቸው በመሆኑ ለአመልካችና ለልጆቻቸው የቤት መስሪያ እንዲሰጣቸው፣ በቀሪው ይዞታ ደግሞ ተገቢው ካሳ እንዲከፈላቸው ዳኝነት በመጠየቃቸው ነው፡፡መልካም ንባብ……..