እነ ወ/ሮ ዘውዲቱ ድንቁ(2ሰዎች)የቀድሞ አርጋፋ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት (በአሁን አርጋፋ ማዘጋጃ ቤት)የሰ/መ/ቁ፡- 250597 እነ ወ/ሮ ዘውዲቱ ድንቁ(2ሰዎች)የቀድሞ አርጋፋ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት (በአሁን አርጋፋ ማዘጋጃ ቤት)የሰ/መ/ቁ፡- 250597 የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች ሐምሌ 03 ቀን 2015ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ.ቁ 26960፤ ጥቅምት 28 ቀን 2015 የሰጠው ውሳኔ እና ይህንኑ ውሳኔ በማጽናት የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 42102፤ ሚያዝያ 03 ቀን 2015ዓ.ም መወሰኑ የመሠረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረባቸው ነው፡፡ ጉዳዩ በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 6 መሠረት የቀረበን የዳግም ዳኝነት ጥያቄን የሚመለከት ሲሆን ከመነሻው በዋናው ጉዳይ ክርክር የተጀመረው በኦሮሚያ ክልል አጋርፋ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን አመልካች ከሳሽ፤ የአሁን ተጠሪ ተከሳሽ ነበሩ፡፡መልካም ንባብ…..
አቶ ኩማ መልኩ እና አቶ ሰለሞን ዘለቀ የሰበር መ/ቁ/250546 አቶ ኩማ መልኩ እና አቶ ሰለሞን ዘለቀ የሰበር መ/ቁ/250546 መዝገቡ ለሰበር ችሎት የቀረበዉ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የስር ፍርድ ቤት ዉሳኔ የህግ ስህተት የለዉም በማለት በመ/ቁ/ 423754 ላይ በቀን 11/09/2015ዓ.ም የሰጠዉ ትእዛዝ የህግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል በዚህ ሰበር ችሎት እንዲታረም በማለት አመልካች ባቀረቡት አቤቱታ መነሻ ነዉ፡፡ የጉዳዩ አመጣጥ ባጭሩ ሲታይ በስር ፍርድ ቤት አመልካቹ ከሳሽ ሲሆን ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን የተከራከሩ ሲሆን ጉዳዩ እርሻ መሬት ይዞታ የሚመለከት ነዉ፡፡አመልካች ሃምሌ 12 ቀን 2014ዓ.ም በዲጋሉና ጢጆ ወረዳ ፍርድ ቤት ባቀረበው አቤቱታ በዲጋሉ አራቢ ቀበሌ ውስጥ የሚገኘውን አዋሳኞቹ በክሱ የተጠቀሰ መሬት ከአያቴ ከበደ ዋቅጅራ እና ሴት አያቴ ወ/ሮ የሺ ተ/ማሪያም በመ/ቁ/43575 በሆነው በዉርስ ተወስኖልኝ በመ/ቁ 43575 ተፈጽሞልኝ እያለ ተጠሪ ምንም መብት ሳይኖረዉ ስለያዘብኝ እንዲለቅልኝ ሲል የጠየቀ ሲሆን ተጠሪ ጥቅምት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ባቀረበው መልስ ይዞታው የአመልካች አያቶች ሳይሆን በቅይይር ከአቶ ታደሰ ከበደ ያገኘሁት የግል ይዞታዬ ነው፤የተቀያየርነውን ይዞታ ሰዎች ተቀብለው የመኖሪያ ቤት የሰሩበት ሲሆን እኔም ይዞታውን እየተጠቀምኩበት ስለሆነ ክሱ ተቀባይነት የለዉም በማለት ተከራክሯል፡፡መልካም ንባብ…..
እነ ወ/ሮ ጌጤ ሙለታ(3ሰዎች) እና ወ/ሮ ብርሃኔ ካባ የሰ/መ/ቁ 249367 እነ ወ/ሮ ጌጤ ሙለታ(3ሰዎች) እና ወ/ሮ ብርሃኔ ካባ የሰ/መ/ቁ 249367 ለዚህ የሰበር አቤቱታ መቅረብ ምክንያት የሆነዉ ጉዳይ የዉርስ ክርክርን የሚመለከት ሆኖ ክርክሩ የተጀመረዉ በአምቦ ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት አመልካቾች ከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ አመልካቾች በአምቦ ወረዳ ፍርድ ቤት በተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ ሟች አባታቸዉን ሙለታ ካባን ተክተዉ ከሟች አያቶቻቸዉ አቶ ካባ ዳባ እና ወ/ሮ ብርቱካን ፈካንሳ በዉርስ ሊያገኟቸዉ የሚገቡ በአምቦ ወረዳ ኢላሙ ጎርሚቲ ቀ/ገ/ማኅበር ዉስጥ በስድስት በተለያዩ ቦታዎች የሚገኙትን የገጠር እርሻ ይዞታዎችን፣ በይዞታዎቹ ላይ የተፈሩ ቋሚ ሀብቶችንና የተለያዩ ከብቶችን ተጠሪ ከድርሻቸዉ በላይ ይዘዉ የሚገኙ መሆናቸዉን ገልፀዉ የዉርስ ሀብቶቹ ተጣርተዉ የሟች አባታቸዉን የዉርስ ድርሻ እንዲሁም ከፊሎቹ ከሳሾች ራሳቸዉን ችለዉ በጥገኝነት ሊያገኙ የሚገባቸዉን የዉርስ ድርሻ እንዲያገኙ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…..
ብርሃን ባንክ አ/ማ እና ብርሃን ባንክ መሠረታዊ የሠራተኞች ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 263727 ብርሃን ባንክ አ/ማ እና ብርሃን ባንክ መሠረታዊ የሠራተኞች ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 263727 የሰበር አቤቱታው የቀረበው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው አመልካች የስር ተከሳሽ ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ ነበር፡፡ ተጠሪ ሐምሌ 26 ቀን 2015 ዓ/ም ጽፎ ባቀረበው ክስ አመልካች ድርጅት ለሁሉም ሰራተኞች በሚል በተጻፈ ጥቅማጥቅም የተወሰነ መሆኑ ተገልጾ እያለ የቤት አበል በተለምዶ በጽሕፈት መደብ ላይ ያልሆኑ /non-clericals/ የሚሰሩ ሰራተኞች አልከፍልም ማለቱ የእኩልነት መብት የሚጥስ በመሆኑ የቤት አበል እንዲከፈል እንዲወሰን ዳኝነት ጠይቋል፡፡ አመልካች በሠጠው መልስ ደብዳቤው ለሁሉም ሠራተኞች በሚል የተጻፈው የተለያየ የጥቅማጥቅም ሁኔታዎች የተካተቱበት ስለሆነ ነው፣ በጽሕፈት መደብ ላይ ላልሆኑ ሰራተኞች የቤት አበል ጥቅማጥቅም አልተወሰነም፣ ጥቅማጥቅም ሳይወሰን ክፍያ እንዲፈጸም ዳኝነት ሊጠየቅበት አይችልም፣ በተመሳሳይ የሥራ መደብ ላይ ለሚሰራ ሠራተኞች የተለያየ ጥቅማጥቅም እንዲያገኙ ያልተወሰነ በመሆኑ የእኩልነት መብትን አልተጣሰም፣ ክሱ ተቀባይነት የለውም በማለት ተከራክሯል፡፡መልካም ንባብ…
ተወልደ ግደይ የኤሌክትሪክ ኬብል እና ዋየር ፋብሪካ እናየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሰ/መ/ቁጥር 262505 ተወልደ ግደይ የኤሌክትሪክ ኬብል እና ዋየር ፋብሪካ እናየኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሰ/መ/ቁጥር 262505 ጉዳዩ ለቅድመ ጥንቃቄ ዕዳን መልሶ የማዋቀር ሥነ ሥርዓትን የሚመለከት ነው፡፡ጉዳዩ የተጀመረው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በአመልካች አቤቱታ አቅራብነት ነው፡፡በአመልካች የቀረበው አቤቱታ ይዘትም በአጭሩ ከተጠሪ ጋር ግንቦት 22 ቀን 2003 ዓ.ም እና ነሀሴ 28 ቀን 2011 በተደረገ የብድር አከፋፈል ስምምነት ብር 692,389,514.50 የብድር ገንዘብ ያለበት መሆኑን፤ብድሩ ተከፍሎ የሚያልቀው የካቲት 27 ቀን 2016 ዓ.ም መሆኑን፤ከዚህ ውሰጥ ብር 419,224,378.70 መክፈሉን፤ ባጋጠመው የውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያት የፋይናንስ እጥረት ያጋጠመው ቢሆንም አሁን የፋይናንስ እጥረት መሰረት የሆነው የጥሬ እቃ አቅርቦት ችግር በመፈታቱ የፋይናንስ ችግሩ በቅርብ የሚቀረፍ መሆኑን እና ይህም በሚዋቀርለት የዕዳ መክፈያ ጊዜ ውስጥ በተጨባጭ ዕዳውን መክፈል የሚያስችለው መሆኑን እንደዚሁም ሌሎች ምክንያቶችን በመዘርዘር ለቅድመ ጥንቃቄ ዕዳን መልሶ የማዋቀር ሥነ ሥርዓት ተፈቅዶለት ዕዳው ተዋቅሮ የሚከፍልበት ጊዜ እንዲሰጠው፤ዕዳው ሊከፈል የሚችልበትን አማራጭ መፍትሄዎች የሚያጠና ለፍ/ቤቱ፤ለአመልካች እና ለተጠሪ እንዲሁም ሌሎች ገንዘብ ጠያቂዎች ድጋፍ የሚያደርግ እና ሪፖርት የሚያቀርብ ባለሙያ እንዲሾም ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…