እነ አቶ ዮሐንስ ገ/ሚካኤል(5ሰዎች) እና ወ/ሮ ሃና ደርሶልኝ(2ሰዎች) የሰበር መዝገብ ቁጥር - 256463 እነ አቶ ዮሐንስ ገ/ሚካኤል(5ሰዎች) እና ወ/ሮ ሃና ደርሶልኝ(2ሰዎች) የሰበር መዝገብ ቁጥር - 256463 አመልካቾች ሚያዚያ 2 ቀን 2015 ዓ.ም በተፃፈ የመቃወም አቤቱታ ሟች አባታቸው አቶ ገ/ሚካኤል ኃ/ማርያም በህይወት እያሉ እንዲሁም አባታቸው ከሞቱ በኃላ በስር ፍርድ ቤት ተጠሪ የሆኑት፣ አመልካቾችና የ 96 አመት የሆኑት የግራ ቀኙ እናት ጋር በአልኮልና በለስላሳ ማከፋፈያ እንዲሁም በሸቀጣሸቀጦች ጅምላ ንግድ ስራ ተሰማርተው በቁጥር ስምንት የሆኑ የተለያዩ ተሸከርካሪዎች፤ ደምቢዶሎ ከተማ ውስጥ የሚገኝ ሆቴል፣ የቡና ማበጠሪያ፣ የመጠጥ ማከፋፈያ፣ የመኖሪያ ቤትና መጋዘን፤ በቡና ግብይት ላይ የነበረ አንድ ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ ብር፣ በአዋሽ ባንክ ያለ 50 የአክስዮን ድርሻ በጋራ ያፈሩ መሆኑንና ተጠሪዎች ጋብቻ ሲፈፅሙ እነዚህ ንብረቶች የአመልካቾች መሆናቸውን በጋብቻ ውላቸው ተስማምተዋል፡፡ እነዚህ ንብረቶች ከፊሎቹ ባሉበት ከፊሎቹ በሽያጭ ሆነ በሌላ መንገድ እየተለዋወጡና እየተቀላቀሉ ብዛታቸው 16 የሆኑ በተጠሪ ስም የተመዘገቡ የማይንቀሳቀሱ ንብረቶች፤ በተጠሪ ስም የተመዘገቡ በአዋሽ ባንክ፣ በኦሮሚያ ባንክ፣ በህብረት ባንክ ያሉ አክስዮኖች፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ በአዋሽ ባንክ፣ በህብረት ባንክ፣ በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ፣ በኦሮሚያ ባንክ ተጠራቅሞ የሚገኝ ገንዘብ እና ተሸከርካሪዎች በቤተሰብ የተፈሩና በተጠሪዎች የጋብቻ ውል ላይም የቤተሰብ ንብረቶች መሆናቸው ተረጋግጦ እያለ ተጠሪዎች ከዚህ በተቃራኒ በሰበታ ከተማ የሚገኘውን በ 612 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ቤት፣ በቄለም ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ የሚገኘውን መኖሪያ ቤት እንዲሁም በዚህ ከተማ በ 2,000 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ ሆቴል ን በመተው ሌሎችን ንብረቶች የተጠሪዎች የጋራ ንብረት ነው በማለት ያስወሰኑ በመሆኑ ውሳኔው ቀሪ እንዲሆን በማለት የመቃወም አቤቱታቸውን አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…
ቻይና ኮሙኒኬሽን ኩባንያ ግንባታ ወንጪ ደንዲ ኢኮቱሪዝም ፕሮጀክት እና ማንዴሳ ጪብሳ የሠ/መ/ቁጥር 256412 ቻይና ኮሙኒኬሽን ኩባንያ ግንባታ ወንጪ ደንዲ ኢኮቱሪዝም ፕሮጀክት እና ማንዴሳ ጪብሳ የሠ/መ/ቁጥር 256412 ጉዳዩ የጉዳት ካሳ ክፍያን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተጠሪ ከሳሽ አመልካች ደግሞ በተከሳሽነት ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ ያቀረቡት ክስ፡- አመልካች ከደንዲ ሀይቅ እስከ ወንጪ ሀይቅ ያለው መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ኮንትራክተር በመሆን በሚሰራበት ወቅት በደንዲ ወረዳ ገ/ጥራንጉ ሹቤሶሌ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ ከሚገኘው ስፋቱ አራት ሄክታር በሆነው የእርሻ ይዞታዬ ላይ መንገድ ለመገንባት የቆፈረውን አፈር ጥቅምት 10 ቀን 2015 ዓ.ም በተሸከርካሪዎች ጭኖ በመድፋት በመሬቱን ገደላማ በማድረግ ከጥቅም ውጪ በመሆኑ በመሬቱ ላይ ተዘርቶ የነበሩትን የሰነፍ ቆሎ፤ገብስ እና ሚስር ቡቃያዎችን፤ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ በቁጥር 5,900.00(አምስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ባህር ዛፍ፤10 እግር ጥድ፤እንዲሁም 900 እግር ቀርከሃ ስላወደመብኝ የእጽዋቶቹ እና የሰብል ግምቱ ለወደፊት ያገኙ የነበረውን የ15 አመት ጥቅም በድምሩ ብር 9,823,000 (ዘጠኝ ሚሊየን ስምንት መቶ ሃያ ሶስት ሺ) የጉዳት ካሳ ከወጪና ኪሳራ ጋር እንዲከፍለኝ ይወሰንልኝ በማለት ከሰዋል፡፡መልካም ንባብ…
እነ አቶ አመድ ሙሜ(2ሰዎች)የእና ወ/ሮ አሚናት ኡስማንሰ/መ/ቁጥር 254020 እነ አቶ አመድ ሙሜ(2ሰዎች)የእና ወ/ሮ አሚናት ኡስማንሰ/መ/ቁጥር 254020 ጉዳዩ የገጠር መሬት ውርስን የሚመለከት ሲሆን ጉዳዩ በጀመረበት የሀረሪ ህዝብ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ ፍ/ቤት የአሁን አመልካቾች ተከሳሽ፤ የአሁን ተጠሪ አውራሽ የሆኑት ወ/ሮ ከዲጃ ዑመር ከሳሽ ነበሩ፡፡ የአሁን ተጠሪ አውራሽ ያቀረቡት ክስም፡- ሟች አባታቸው በ1966 ዓ.ም በሞት የተለዩ መሆኑን፤ሟች አባታቸው እርሳቸውንና ሟች ወንድማቸውን አቶ ዘከሪያ ኡመር የወለዱ መሆኑን፤ሟች ወንድማቸውም የአሁን አመልካቾችን እናት አግብቶ ሲኖር ቆይቶ ልጅ ሳይወልድ እና ሳይናዝ የሞተ መሆኑን፤ ለክርክር መነሻ የሆነው በአራት ቦታ የሚገኘው የገጠር መሬት የሟች አባታቸው እና ክፍፍል ያልተፈጸመበት እንዲሁም ከሟች ወንድማቸው ጋር ሲጠቀሙበት የቆዩ መሆኑን፤ ሟች ወንድማቸው ከሞተ በኋላም የአሁን አመልካቾች እናት እየረዳቻቸው በመሬቱ ስትጠቀም እንደነበር፤ እርሷ ከሞተች በኋላ መሬቱን ተጠሪዎች እንዲለቁ ቢጠየቁ ፈቃደኛ ሊሆኑ አለመቻላቸውን ጠቅሰው መሬቱን ለቀው እንዲያስረክቡኝ እና ከመሬቱ የተገኘውን ጥቅም ጨምረው እንዲከፍሉኝ የሚል ነበር፡፡ ተጠሪዎች ለክሱ ባቀረቡት መልስ ክሱ በይርጋ የተቋረጠ ነው፡፡ ለክርክር መነሻ የሆነውን መሬት እናታችን መብት በመመስረት ንብረትነቱ የመንግስት በሆነ መሬት ላይ ከከሳሽ ወንድም ጋር ባልና ሚስት በመሆን ጋብቻው በሞት ቀሪ እስከሆነበት ጊዜ ድረስ መብት ፈጥረው እየተጠቀሙ የቆዩ በመሆኑ ክሱ ውድቅ እንዲደረግልን በማለት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ….
ጠቋሬ ፈለቀ እና አባ ምትኩ ዘዉዴ የሰ.መ.ቁ.253916 ጠቋሬ ፈለቀ እና አባ ምትኩ ዘዉዴ የሰ.መ.ቁ.253916 ይህ የአፈጻጸም ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል በዳህና ወረዳ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁን አመልካች የሥር ፍርድ ባለመብት፣ የአሁን ተጠሪ የሥር የፍርድ ባለዕዳ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር፡፡ ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ አመልካች የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ.0337693 ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ፡፡ የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ በግራ ቀኛዉ መካከል በነበረዉ የይዞታ ክርክር የሥር የወረዳዉ ፍ/ቤት የአሁን ተጠሪ ለክርክር መነሻ የሆነዉን ይዞታ ለቆ ለአመልካች እንዲያስረክብ መወሰኑን መዝገቡ ያሳያል፡፡ የአሁን አመልካች ፍርዱን ለማስፈጸም የአፈጻጸም አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን የወረዳዉ ፍ/ቤቱ የአሁን አመልካች በይዞታዉ ላይ ባለመብት ከመሆኑ በፊት የአሁን ተጠሪ በይዞታዉ ላይ ሁለት ክፍል ያለዉን ቤት መስራቱን በማረጋገጥ አመልካች የቤቱን ግምት ለተጠሪ እንዲከፍልና ተጠሪ ይዞታዉን ለቆ ለአመልካች እንዲያስረክብ ብይን መስጠቱን የዉሳኔዉ ግልባጭ ያመለክታል፡፡ በየደረጃዉ ያሉት የክልሉ ፍ/ቤቶችም የቀረበላቸዉን ቅሬታ ዉድቅ በማድረግ የሥር ፍ/ቤትን ዉሳኔ በማጽናት መወሰናቸዉን የሥር ፍ/ቤት የዉሳኔ ግልባጭ ያሳያል፡፡ የአሁን የሰበር አቤቱታ የቀረበዉ በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ለማስለወጥ ነዉ፡፡ የአሁን አመልካች መስከረም 4 ቀን 2016 ዓ.ም በተጻፈ የሰበር አቤቱታ፡ የአሁን ተጠሪ በዋናዉ ጉዳይ ላይ ተከራክሮ የቤት ግምት ካሳ እንዲከፈለዉ የፍርድ ባለመብት ባልሆነበት የሥር ፍ/ቤት በዋናዉ ፍርድ የቤት ግምት ካሳ ጉዳይ ለተጠሪ እንዲከፈል ባልተወሰነበት፣ ተጠሪ በይዞታዉ ላይ በሕገወጥ መንገድ ቤቱን ሲሰራ አመልካች እየተቃወምኩት መሆኑን ተረጋግጦ ባለበት የሥር ፍ/ቤት በዋናዉ ፍርድ መሰረት ለክርክር መነሻ የሆነዉን 10 በ15 ካ.ሜ የሆነዉን ይዞታ ተጠሪ ለአመልካች እንዲለቅ ማስፈጸም ሲገባዉ አመልካች ለተጠሪ የቤቱን ግምት እንዲከፍል መወሰኑ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ እንዲታረምልኝ በማለት በዝርዝር አመልክቷል፡፡መልካም ንባብ….
እስጢፋኖስ /ዩቡና/ ዲራጎ እና የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሠ/መ/ቁጥር 251519 እስጢፋኖስ /ዩቡና/ ዲራጎ እና የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሠ/መ/ቁጥር 251519 አመልካች በቀን 26/11/2015ዓ/ም የተጻፈ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት መጽናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለት ሲሆን ይዘቱ በአጭሩ - አመልካች ድርጊቱ በተፈጸመበት ቦታ ነበርኩኝ እንጂ ድርጊቱን አልፈጸምኩም፤ የተጠሪ ምስክሮች ድርጊቱን ስለመፈጸሜ አላስረዱብኝም፤ ባቀረብኩት ምስክር ወንጀሉን ያልፈጸምኩ መሆኑን አስረድቻለሁ፤የተጠሪ ምስክሮች እርሱን ይመስላል ከማለት ውጪ ድርጊቱን ስለመፈጸሜ አላስረዱም፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠዉን ዉሳኔ በማጽናት የወሰነዉ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 23/2 ስር በተደነገገዉ መሠረት የግድያ ወንጀል መፈጸሜ ሳይረጋገጥ በመሆኑ ዉሳኔዉ ከዚህ ድንጋጌ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ በሰ/መ/ቁጥር 22069 ስር የተሰጠዉን አስገዳጅ የሕግ ትርጉም የሚቃረን ነዉ፡፡ስለሆነም ተጠሪ ያቀረባቸው ምስክሮች አመልካች ድርጊቱን ስለመፈጸሜ ከጥርጣሬ በላይ ያላስረዱ ስለሆነ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ ተሽሮ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ እንዲጸናል፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠዉ የጥፋተኝነት ውሳኔው የሚያጸና ከሆነም አንቀጹ ወደ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 540 እንዲቀየርልኝ እና የ3ኛ አመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ስለሆንኩ ቅጣቱ በወ/ህ/አንቀጽ 192 መሰረት እንዲገደብልኝ በማለት አመልክቷል፡፡መልካም ንባብ….