Login
  • Register
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • Message from the President
    • History and Traditions
    • Vision Mission and Mandate
    • President
      • Current President
      • Former Presidents
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • Judges
      • Current
      • Former Judges
    • Judicial Administration Council
    • Court Administration & Directorates
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • E-Filing
    • Quick Start Guide
      • Registration
      • E-Filing
    • User Guide
    • Rules and Guidelines
    • Forms
    • Tutorials
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Auction
ግሩም ሆስፒታል ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና ዶ/ር ተስፋዬ አልማው የሰ/መ/ቁ. 219386

ግሩም ሆስፒታል ኃ/የተ/የግ/ማህበር እና ዶ/ር ተስፋዬ አልማው የሰ/መ/ቁ. 219386

ጉዳዩ የስራ ስንብትን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪ በአመልካች ላይ ጽፈው ባቀረቡት ክስ በአመልካች ሆስፒታል ውስጥ በኤክስፐርት ሜዲካል ስፔሻሊስት (ሰርጀሪ) የስራ መደብ ላይ በወር ብር 49,000.00፣ ሃርድሺፕ አሎዋንስ 19,124.00፣ እንዲሁም ለእያንዳንዱ የቀዶ ጥገና ህክምና ብር 1,000.00 እየተከፈላቸዉ ከቀን ግንቦት 07 ቀን 2009 ዓ.ም ጀምሮ ሲሰሩ ከቆዩ በኋላ አመልካች የካቲት 19 ቀን 2013 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ የሁለት ወር የማስጠንቀቂያ ጊዜ በመስጠት ከስራ ከህግ ውጪ ከስራ ያሰናበታቸዉ መሆኑን ጠቅሰዉ የተለያዩ ክፍያዎች እንዲከፈላቸዉ ይወሰንላቸዉ ዘንድ የጠየቁትን  ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ፡፡መልካም ንባብ……

እነ አቶ ኃብተወልድ ተከተለው እና ህዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር የሰበር መ/ቁ/ 218918

እነ አቶ ኃብተወልድ ተከተለው እና ህዳሴ ቴሌኮም አክሲዮን ማህበር የሰበር መ/ቁ/ 218918

ጉዳዩ የደረጃ እድገት የሚመለከት ነዉ፡፡ክርክሩ የተጀመረው በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የደ/ብርሃን ከተማ ወረዳ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካቾች ከሳሽ በመሆን በአሁኑ ተጠሪ ላይ ባቀረበቡት ክስ ተጠሪ ሚያዝያ 10 ቀን 2011 ዓ.ም ባወጣው የደረጃ እድገት እና የዝውውር ማስታወቂያ ለመወዳደር በተለያየ ስራ መደብ ላይ ተመዝግበን የነበርን ቢሆንም ተጠሪ ግን የአከባቢ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ የስራ መደብ ላይ ብቻ የደረጃ እድገት አወዳድሮ ተፈፃሚ ያደረገ ሲሆን አመልካቾች ለመወዳደር ከተመዘገብንበት መደብ ላይ ያለ አግባብ ከደረጃ እድገት እና ዝውውር መታገዳችን ህገወጥ በመሆኑ በደረጃ እድገቱና ዝውውሩ ላይ ተሳታፊ እንዲንሆን ውሳኔ ይሰጥልን በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ……..

አቶ መሃሪ አለምሶም እና የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ዓቃቤሕግ የሰ.መ.ቁ 218822

አቶ መሃሪ አለምሶም እና የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ዓቃቤሕግ የሰ.መ.ቁ 218822

የአሁን ተጠሪ በስር ፍርድ ቤት በአሁን አመልካች ላይ ያቀረበው ክስ ይዘት በአጭሩ፡- አመልካች የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 693(1)ን በመተላለፍ በቀን 20/03/2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት በሚሆንበት ጊዜ በሀዋሳ ከተማ መሃል ክፍለ ከተማ ንጋት ኮከብ ሆቴል ውስጥ ልዩ ቦታው አረብ ሰፈር በሚባልበት ከግል ተበዳይ ሉቻ ተክሉ የምትነግድበት ሥራ ቦታ ድረስ በመሄድ በኦሮሚያ ክልል እና ሲዳማ ክልል የቢሮ ዕቃዎች ለማስገባት ጨረታውን ስላሸነፍኩ ብር ቸግሮኛል በጋራ እንሰራለን ብር አበድሪኝ በማለት በተለያየ ቀን ዕቃዎችን ለመግዛት ብሎ በካሽ እና በአካውንት የወሰደውን ብር በንግድ ባንክ በሁለት ግዜ እንዲከፈል ሲል ቼክ ቁጥር BC19664274 በሆነው 1,600,000 (አንድ ሚሎዮን ስድስት መቶ ሺህ ብር) ቀን 30/3/2013 ዓ.ም ጽፎ የሰጠ በመሆኑ እንዲሁም በቼክ ቁጥር BC19664275 በሆነው 1,500,000 (አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺህ ብር) በቀን 15/4/2013 ዓ.ም  ጽፎ በመስጠት በአጠቃላይ ብር 3,100000 (ሶስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሺህ ብር) የሚሆን በአመልካች ስም በተከፈተ የባንክ ሂሳብ ውስጥ በቂ ገንዘብ እንደሌለ አጣርቶ መረጃ የተሰጠ በመሆኑ በቂ ስንቅ ሳይኖር  ቼክ በማዘዙ ተከሷል የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…….

ማልድ የትምህርት ድጋፍ ሰጪ ኃ/የተ/የግ/ማህበርበ እናወ/ሪት ብሔር ዮናስ የሰ/መ/ቁ. 218123

ማልድ የትምህርት ድጋፍ ሰጪ ኃ/የተ/የግ/ማህበርበ እናወ/ሪት ብሔር ዮናስ የሰ/መ/ቁ. 218123

ጉዳዩ የተጀመረውም በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠሪ ባቀረበችው ክስ በአመልካች ድርጅት ውስጥ ከመስከረም 04 ቀን 2009 ዓ.ም ጀምሮ በወር ብር 27,000.00 እየተከፈለኝ በመምህርነት፣ በረዳት አስተዳዳሪነት በልዩ ፍላጎት ዲፓርትመነት የአስተዳደርና ትምህርት ድጋፍ ሰጪ ኃላፊ የስራ መደብ በመሪነት፣ እንዲሁም ሰላሳ በመቶ የሚሆነውን አስተዳደራዊ ስራ እየሰራሁ ያለበቂ ምክንያት የስራ ውሌን ያቋረጠ በመሆኑ ስንብቱ ህገ-ወጥ ነው ተብሎ አመልካች ልዩ ልዩ ክፍያዎች እንዲከፍለኝ ይወሰንልኝ በማለት የጠየቁትን ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ፡፡ አመልካች በበኩሉ ተጠሪ የልዩ ፍላጎት ዲፓርትመንት የአስተዳደርና ትምህርት ድጋፍ ሰጪ ኃላፊ የስራ መደብ በመሪነት እንዲሁም ሰላሳ በመቶ የሚሆነውን አስተዳደራዊ ስራ ሲሰሩ የቆዩ የስራ መሪ በመሆናቸዉ የስራ ክርክር ችሎት ጉዳዩን አይቶ የመወሰን የስረ ነገር ስልጣን የለውም የሚል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አቅርቧል፡፡መልካም ንባብ…….

ስንታየሁ የግል 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና እነ አቶ ይርጋ ባይችሉ የሰ/መ/ቁ. 217836

ስንታየሁ የግል 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና እነ አቶ ይርጋ ባይችሉ የሰ/መ/ቁ. 217836

ጉዳዩ የግል የስራ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በደብረማርቆስ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች ባቀረቡት ክስ በአመልካች ትምህርት ቤት በመምህርነት ተቀጥረዉ በመስራት ላይ እያሉ ከነሐሴ 25 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ አመልካች ወደ ትምህርት ቤቱ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከልና ወደ ፖሊስ ሄዳችሁ ከሳችሁኛል በሚል ምክንያትም ማስጠንቀቂያ ሳይሰጣቸዉ ከስራ እንዲሰናበቱ ያደረገበት አግባብ ህገ ወጥ መሆኑን ጠቅሰዉ አመልካች ወደ ስራ እንዲመልሳቸዉ፣ ወደ ስራ የማይመለሱበት ምክንያት ካለም የተለያዩ ክፍያዎች እንዲከፍላቸዉ እንዲሁም ለስራ ግብርና ለጡረታ በሚል ከደመወዛቸዉ ሲቀንስ የነበረዉን ለሚመለከታቸዉ አካላት ገቢ እንዲያደርግ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ……  

12345678910NextLast
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us 
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions