እነ ወ/ሮ አስካለ ካሳ ገ/ሥላሴ እና ወ/ሮ አልማዝ ሀብታሙ ገ/ሥላሴ የሠ/መ/ቁጥር 248877 እነ ወ/ሮ አስካለ ካሳ ገ/ሥላሴ እና ወ/ሮ አልማዝ ሀብታሙ ገ/ሥላሴ የሠ/መ/ቁጥር 248877 ጉዳዩ አባትነትን የመካድ ክስ ሊቀርብ የሚችልበትን አግባብ የሚመለከት ነዉ፡፡አመልካቾች በአሁን ተጠሪ እና በስር 2ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ ጌጤ በየነ ወያ ላይ በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመሰረቱት ክስ - አመልካቾች የሟች ወንድማችን አስር አለቃ ሀብታሙ ካሳ ገብረስላሴ ተተኪ ወራሾች መሆናችንን በፍርድ ቤት አስወስነናል፡፡በዚህ መሠረት አመልካቾች የሟች ወንድማችን ዉርስ እንዲጣራ አቤቱታ አቅርበን ዉርሱ በማጣራት ሂደት ላይ ተጠሪ የሟች አስርአለቃ ሀብታሙ ካሳ እና ከሚስታቸዉ የስር 2ኛ ተከሳሽ ሳይወለዱ ልጅ ነኝ በማለት ከሕግ-ዉጭ ከአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመ/ቁጥር 1235/98 ላይ በቀን 17/08/1998 ዓ/ም የወራሽነት ማስረጃ መዉሰዳቸዉን አረጋግጠናል፡፡ሟች አስር አለቃ ሀብታሙ ካሳ ገ/ስላሴ በሕይወት ዘመናቸዉ ከ2ኛ ተከሳሽ ከወ/ሮ ጌጤ በየነ ወያ ጋር ጋብቻ መስርተዉ ይኖሩ የነበረ ቢሆንም ከአብራካቸዉ ልጅ አልወለዱም፡፡ወ/ሮ ጌጤ የተጠሪ እናት አይደሉም፡፡ ሆኖም 1ኛ ተጠሪ የሟች የአስር አለቃ ሀብታሙ ካሳ ባለቤት ከሆኑት ወ/ሮ ጌጤ በየነ ጋር የስጋ ዝምድና ስላላቸዉና ሟችም ስላሳደጓቸዉ ብቻ ልጅ ነኝ በማለት እንቅስቃሴ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ስለሆነም ተጠሪ የሟች አስር አለቃ ሀብታሙ ካሳ ገ/ስላሴ ልጅ አይደሉም ተብሎ ይወሰንልን በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…
ጉምሩክ ኮሚሽን ባህርዳር ቅ/ጽ/ቤት እና አቶ ሀይለማርያም መለስ የሰ.መ.ቁ 252361 ጉምሩክ ኮሚሽን ባህርዳር ቅ/ጽ/ቤት እና አቶ ሀይለማርያም መለስ የሰ.መ.ቁ 252361 ጉዳዩ ያልተከፈለን የቀረጥና ታክስ ክፍያ መሠረት በማድረግ ወለድ ሊከፈል አይገባም በማለት የቀረበን ክርክር የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው ከፌዴራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ነው፡፡ የአሁን ተጠሪ ለአመልካች መስሪያ ቤት ባቀረቡት አቤቱታ አመልካች መስሪያ ቤት የአሲኩዳ ሲስተም ኤክሳይዝ ታክስ የማይከፈልባቸው ዕቃዎች ላይ ከጉምሩክ ቀረጥ ማስከፈያ ዋጋ መነሻ ወደ ተጨማሪ እሴት ታክስ ሲሸጋገር 1 በመቶ ሲቀንስ የነበረ በመሆኑ በሲስተም ችግር ምክንያት የተዘለለውን ቀሪ ቀረጥ እና ታክስ ተጠሪ እንዲከፍል ጠይቋል፤ ተጠሪ ቀረጥ እና ታክሱ እንዳይከፈል ያደረግኩት ነገር የለም፤ አመልካች ቀረጥ እና ታክሱን ማስከፈል ይችላል ቢባል እንኳን ወለድ መታሰቡ ከጉምሩክ አዋጅ ውጪ ስለሆነ ውሳኔው ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ…
አቢብ አብዱላሂ እና ሙና አብዲ የሰ/መ/ቁጥር 261889 አቢብ አብዱላሂ እና ሙና አብዲ የሰ/መ/ቁጥር 261889 አቤቱታውም እርስ በእርስ በሚጋጭ ማስረጃ የተወሰነ ውሳኔ የሰበር አስገዳጅ የሕግ ትርጉምን የጣሰ ነው፡፡ የእርሳ ይዞታ በክልሉ ሕግ ለልጅ ልጅ አይደገምም ስጦታውም አልተመዘገበም፡፡ ስለዚህ ይታረምልኝ የሚል ነው፡፡ጥሩ ንባብ.....
እነ አቶ ዮሀንስ ይማም እና የኢትዮጲያ መድሀኒት ፋብሪካ የሰበር መ/ቁ/255052 እነ አቶ ዮሀንስ ይማም እና የኢትዮጲያ መድሀኒት ፋብሪካ የሰበር መ/ቁ/255052 ጉዳዩ የስራ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን አቤቱታውም በወቅቱ ህገወጥ ስብሰባ ስለማድረጋችን በተጠሪ ምስክሮችም ቢሆን አልተረጋገጠም የተረጋገጠው የመብት ጥያቄ ማንሳታችን ነው ይህ ደግሞ ያለማስጠንቀቂያ የስራ ውል ለማቋረጥ በቂ ምክንያት አይደለም ስለሆነም የስር መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዚህ አግባብ መርምሮ የሰጠውን ውሳኔ የስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመሻር የሰጠው ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊሻርልን ይገባል የሚል ነዉ፡፡ጥሩ ንባብ
ወ/ሮ ፎዚያ ከድር ዓሊ እና ወ/ሮ ሕይወት ደምሴ ወልዴ የሰ/መ/ቁ.254503 ወ/ሮ ፎዚያ ከድር ዓሊ እና ወ/ሮ ሕይወት ደምሴ ወልዴ የሰ/መ/ቁ.254503 መዝገቡ ለዚህ ሰበር ሰሚ ችሎት የቀረበው የሰበር አጣሪ ችሎት በጥር 28 ቀን 2016 ዓ.ም በዋለው ችሎት ጉዳዩ በሰበር ሰሚ ችሎት እንዲታይ በመምራቱ ነው፡፡መልካም ንባብ፡፡