ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398 ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398 የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ ስድስት) ካርቶን የተለያዩ የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ከቻይና ተጓጉዘው ሞጆ ደረቅ ወደብ እስኪደርሱ ድረስ ጉድለትን ጭምሮ ለሚደረስ ማንኛውም ጉዳት በመድን ፖሊስ ቁጥር GU/34/2011/2019/00114 አጠቃላይ የመድህን ሽፋን የሰጣቸው ዕቃዎች ሞጆ ደረቅ ወደብ ደርሰው ከሳሽ ከመረከቡ በፊት ዕቃዎች ገበያ ላይ በመታየታቸው ፍተሻ ተደርጎ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት እንዲፈፀም ህዳር 15 ቀን 2012 ዓ.ም ከሳሽ አቤቱታ አቅርቦ የጉምሩክ ጽ/ቤት ተወካይ፤አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት እና የከሳሽ ማኅበር ተወካዮች በተገኙበት ህዳር 17 ቀን 2012 ዓ.ም ዕቃዎቹ የመጡበት ኮንቴነር ተከፍቶ ሲፈተሸ የዋጋ ግምታቸው ብር 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) የሆነ 171 እሽግ መጉደሉ ተረጋግጦ አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የጎደሉ ዕቃዎችን በዝርዝር በመያዝ ወደ መጋዘኑ ማስገባቱንና ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ አጓዡ ኃላፊነት ወስዶ የጉድለት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ስላልሰጠው የካሳ ክፍያ ጥያቄውን ማስተናገድ አልችልም ማለቱን ጠቅሶ ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ በገባው የማሪን ውል መሰረት የጎደሉ ዕቃዎች ዋጋ 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) ካሳ ማስጠንቀቂያ ከደረሰው ከግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ፤ ከወጪ እና ኪሳራ ጭምር እንዲከፍለው ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ….
ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398 ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ እና ኤም.ኢ.ኤስ.ፒ. አፍሪካ ኃ.የተ.የግ. ማህበር ፤የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የሠ/መ/ቁጥር 251398 የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- ከቻይና ሀገር ለሚያስመጣቸው ብራንዳቸው ችንት የዋጋ ግምታቸው ብር 4,899,067.12 (አራት ሚልዮን ስምንት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሺህ ስልሳ ሰባት ከ12/100) የሆኑ1,176(አንድ ሺህ አንድ መቶ ሰባ ስድስት) ካርቶን የተለያዩ የኤሌክትሮኒክ ዕቃዎች ከቻይና ተጓጉዘው ሞጆ ደረቅ ወደብ እስኪደርሱ ድረስ ጉድለትን ጭምሮ ለሚደረስ ማንኛውም ጉዳት በመድን ፖሊስ ቁጥር GU/34/2011/2019/00114 አጠቃላይ የመድህን ሽፋን የሰጣቸው ዕቃዎች ሞጆ ደረቅ ወደብ ደርሰው ከሳሽ ከመረከቡ በፊት ዕቃዎች ገበያ ላይ በመታየታቸው ፍተሻ ተደርጎ የጉምሩክ ሥነ ሥርዓት እንዲፈፀም ህዳር 15 ቀን 2012 ዓ.ም ከሳሽ አቤቱታ አቅርቦ የጉምሩክ ጽ/ቤት ተወካይ፤አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት እና የከሳሽ ማኅበር ተወካዮች በተገኙበት ህዳር 17 ቀን 2012 ዓ.ም ዕቃዎቹ የመጡበት ኮንቴነር ተከፍቶ ሲፈተሸ የዋጋ ግምታቸው ብር 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) የሆነ 171 እሽግ መጉደሉ ተረጋግጦ አጓዡ የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ አገልግሎት ድርጀት የጎደሉ ዕቃዎችን በዝርዝር በመያዝ ወደ መጋዘኑ ማስገባቱንና ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ አጓዡ ኃላፊነት ወስዶ የጉድለት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ስላልሰጠው የካሳ ክፍያ ጥያቄውን ማስተናገድ አልችልም ማለቱን ጠቅሶ ተከሳሹ ህብረት ኢንሹራንስ አ.ማ በገባው የማሪን ውል መሰረት የጎደሉ ዕቃዎች ዋጋ 1,827,753.64 (አንድ ሚልዮን ስምንት መቶ ሃያ ሰባት ሺህ ሰባት መቶ ሃምሳ ሶስት ከ64/100) ካሳ ማስጠንቀቂያ ከደረሰው ከግንቦት 28 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ሕጋዊ ወለድ፤ ከወጪ እና ኪሳራ ጭምር እንዲከፍለው ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ….
ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942 ሲሲኢሲሲ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ እና አቶ ቤልሻጽር ሀይለልዑል መ/ጽድቅ የሰ.መ.ቁ.250942 ይህ የስራ ስንብት ክርክር የተጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁን አመልካች የሥር ከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር፡፡ ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ አመልካች የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ.ቁ.296508 በ29/10/2015 ዓ.ም የሰጠዉ ፍርድ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልን በማለት በማመልከቱ ነዉ፡፡ የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ የአሁን አመልካች በሥር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ባቀረበዉ የክስ አቤቱታ፡ አመልካች በተጠሪ ድርጅት በብሮ ስራ መሃንዲስ የሥራ መደብ ተቀጥሬ በወር 80,000 (ሰማንያ ሺህ) እየተከፈለኝ በአርሲ ሮቤ ዋቤ ሪቨር ፕሮጀክት ሲሰራ የቆየሁ ሲሆን ተጠሪ በ02/12/2014 ዓ.ም በሕገወጥ መንገድ ከሥራዬ ስላሰናበተኝ ተገቢ ክፍያዎችን እንዲከፍለኝ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡መለካም ንባብ….
እነ አቢብ አብዲ (3) ሰዎች እነ ዓሊ ዮሜ ዩሱፍ የሰ/መ/ቁጥር---250757 እነ አቢብ አብዲ (3) ሰዎች እነ ዓሊ ዮሜ ዩሱፍ የሰ/መ/ቁጥር---250757 ክስ ይዘት በአጭሩ: - ለ60 ዓመት በይዞታቸዉ ስር አድርገዉ ጫት በመትል፤ ቦቆሎና ማሽላ እየዘሩ ሲጠቀሙበት ነበረዉን በጅግጅጋ ከተማ አስተዳደር ቀበሌ 20 ዉስጥ የሚገኘዉን ስፋቱ 60 ቆጢ የእርሻ መሬት ይዞታቸዉን በኃይል ወረራ በማድረግ አመልካቾች ይዘዉት በፀጥታ አስከባሪዎች እንዲያቆሙ ትዕዛዝ ቢሰጣቸዉም ከድርጊታቸዉ ሳይገቱየዘሩት እህል በከፊል አዉድመዋል፡፡ ስለሆነም አመልካቾች የፈጠሩት ሁከት እንዲወገድላቸዉ እንዲወሰን የሚጠይቅ ነዉ፡፡መልካም ንባብ….
ወ/ሮ አዳነች ሞኝነት እና አቶ ይልቃል አቤ የሰ.መ.ቁ 250332 ወ/ሮ አዳነች ሞኝነት እና አቶ ይልቃል አቤ የሰ.መ.ቁ 250332 ለዚህ የሰበር ክርክር ምክንያት የሆነው ክርክር የተጀመረው በአማራ ክልል ባሶ ሊበን ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳው ፍርድ ቤት ተጠሪ ከሳሽ አመልካች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ በባሶ ሊበን ወረዳ ፍርድ ቤት ላይ ባቀረቡት ክስ አመልካች የተጠሪ አያት የሟች እማሆይ ጥሩ በላይ የቤተሰብ አባል ሳትሆንና ከሟቿ ጋር በአንድ ላይ ሆኖም ሆነ ከውጭ ሆኖ ሟቿን ሳትጦርና ሳትንከባከብ እንደጦረች እንደተንከባከበችና የሟቿ የቤተሰብ አባል እንደሆነች አስመስላ የሟቿን የእድሜ ባለፀጋነትን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም ሟቿ ከቢሮ ሳይሄዱ እንደሄዱና በስጦታ እንዳስተላለፉላት በማድረግ ከመሬት ባለሙያ ጋር በመመሳጠር በ13/10/1998ዓ.ም የስጦታ ውል በማስሞላት የኑዛዜ ስጦታውን በመሬት አስተዳደር ጽ/ቤት በማስመዝገብ የኑዛዜ ስጦታ አለኝ በማለት አጭበርብራ ማስረጃ እንደያዘች” ገልጸው የመሬት ስጦታ ውሉም ሆነ ማስረጃው እንዲሰረዝላቸው ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….