135
ለሰበር አቤቱታው መነሻ የሆነው ጉዳይ ዋስትናን የሚመለከት ነው፡፡ የአሁን ተጠሪ በአሁን አመልካች ላይ ያቀረባቸው ክሶች 3 ሲሆኑ ይዘታቸውም፡- በ1ኛ ክስ፡- አመልካች የወንጀል ሕጉን አንቀጽ 692/1ድንጋጌን የተላለፍ ራሱን የሐይማኖት አባት በማስመሰል የግል ተበዳይ ወ/ሮ ታርኳ ገብረማሪያምን አታሎ ጽሎት አድርጌ ገንዘብሽን አበዛዋለሁ በማለት ብዛቱ 175,000 የአሜሪካን ዶላር ብር 12,162,2500 ብር በመውሰድ የተሰወረ በመሆኑ በፈጸመው የማታለል ወንጀል ፈጽሟል፤ በ2ኛ ክስ፡- አመልካች የአዋጅ ቁጥር 780/2005 አንቀጽ 29/1/ሀ ድንጋጌን በመተላለፍ በ1ኛ ክስ በፈጸመው የወንጀል ተግበር ያገኘውን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ አቅርቧል፤ በ3ኛ ክስ፡- አመልካች የወንጀል ሕጉን አንቀጽ 385/1/ለ ድንጋጌን በመተላለፍ ሐሰተኛ መታወቂያ በማዘጋጀት ተገልግሎታል የሚሉ ናቸው፡፡መልካም ንባብ…
92
የአሁን አመልካች በስር ፍርድ ቤት በአሁን ተጠሪ ላይ ባቀረቡት ክስ በተጠሪ ኢንሹራንስ ኩባንያ ውስጥ ከመስከረም 08 ቀን 2012 ዓም ጀምሮ እስከ ሀምሌ 22 ቀን 2013 ዓም ድረስ ሲሰሩ ቆይተው የስራ ውላቸውን በፈቃዳቸው ሀምሌ 22 ቀን 2013 ዓም ያቋረጡ መሆኑን ገልፀው ከሰኔ 30 ቀን 2012 ዓም እስከ ሀምሌ 01 ቀን 2013 ዓም ላለው በጀት አመት ተጠሪ ላገኘው ትርፍ የትርፍ አስተዋፆኦ ለኩባንያው ሰራተኞች የሁለት ወር ደመወዝ የከፈለ መሆኑን በመጥቀስ በዚህ ዓመት ለተገኘው ትርፍ የበኩላቸውን አስተዋፆኦ ያደረጉ መሆኑን በማመልከት ከሌሎች ክፍያዎች በተጨማሪ ቦነስ ብር 26,360.00እንዲከፈላቸው እንዲወስንላቸው ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ….
64
ጉዳዩ ንብረት እና ይዞታን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በምዕራብ ወለጋ ዞን የነጆ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን አመልካቾች ከሳሾች፤ የአሁን ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የአሁን አመልካቾች በሥር ፍ/ቤት ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ፡- ሟች አባታችን አቶ በላይ ስመኝ በሀይለስላሴ ዘመን አፍርቶ ሲጠቀምበት የነበረ እና በ1997 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ሲለይ አብረን እየተጠቀምንበት ያለውን በነጆ ከተማ ቀበሌ 04 ውስጥ አዋሳኙ በክሱ በተገለጸ ይዞታ ውስጥ የሚገኝ ብዛቱ 5000 ግምቱ ብር 30000 የሚያወጣ የቡና ተክል፤ በተጠቀሰው ይዞታ ውስጥ በ2011 ዓ.ም የሰራነውን አጠቃላይ ግምቱ ብር 100000 የሚያወጣ አራት ክፍል ሰርቪስ ቤት ተጠሪ በማናውቀው ሁኔታ እማኞችን በማሰማራት በምስራቅ እና በሰሜን አቅጣጫ አጥር በማጠር ስለያዝችብን አጥሩን አንስታ እንድትለቅ ይወሰንልን በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡መልካም ንባብ…..
57
ክርክሩም በተጀመረበት በጋምቤላ ከተማ መስተዳደር የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ተጠሪዎች ከሳሾች እና አመልካች ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ለክርክሩ መነሻ የሆነዉ ተጠሪዎች በአመልካች ላይ ያቀረቡት ክስ ስሆን ይዘቱም በአጭሩ፡በአመልካች ድርጅት ውስጥ ተጠሪዎች ተቀጥረው ለሰባት አመት ከአራት ወር በማንተር የስራ መደብ ላይ እየሰሩ እንደሚገኙ እና በአሰሪና ሰራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/11 መሰረት አንድ ሰራተኛ የሙከራ ጊዜውን ጨርሶ እስካልተሰናበተ ድረስ ቀጣሪው አካል እንደ ቋሚ ሰራተኛ ያላቸውን መብትና ግዴታ እንደሚኖራቸው የሚደነግግ መሆኑን፡፡ሆኖም የአመልካች ድርጅት ተጠሪዎች በስራ ውላችን መሰረት የሙከራ ጊዜያችንን የጨረስን ቢንሆንም ወደ ቋሚነት ያልቀየረን በመሆኑ ቋሚ ሰራተኛ እንድንሆን እና በህገመንግስቱ አንቀፅ 25 መሰረት ከሰራተኛ ጋር እኩል መብታችን ተጠብቆ የ2007 ዓ/ም፤2009 ዓ/ም፤ 2011 ዓ/ም፤ የ2012 ዓ/ም እና 2013 ዓ/ም የሚገባንን ቦነስ ከሐምሌ 1/2013 ዓ/ም ጀምሮ ያልተከፈለንን የበረሃ አበል እና የውሎ አበል እንዲሁም የስራ ሴፍቲዎች እንዲሟላልን ቋሚ ሰራተኛ እንድንሆን ይወሰንልን በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ጥሩ ንባብ…
43
የጉዳዩ አመጣጥ ተጠሪ በስር የፌ/መ/ደ/ፍ/ቤት በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስ በኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ በቀድሞው ወረዳ 24 ቀበሌ 14 አዲሱ ወረዳ 07 ልዩ ስሙ እንፎ መኪና ማሰልጠኛ ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ውስጥ የሚገኝ ከአባቴ አቶ ኩምሳ በዳዳ በውርስ ያገኘሁት እና በግምት 1000ካ.ሜ የሆነ በአራቱም አቅጣጫ መንገድ የሚያዋስኑትን ወላጅ አባቴ ከ1971ዓ.ም እስከ 1991ዓ.ም ድረስ የመንግስት ግብር እየገበረ ቆይቶ ከወላጅ አባቴ ሞት በኋላ እስከ 2011ዓ.ም ድረስ የመሬት ግብር እየገበርኩበት የሚገኝ የሰነድ አልባ ይዞታ ያለኝ ሲሆን በዚህ ይዞታ በ1997ዓ.ም በተነሳው ጂአይኤስ ላይ ግንባታው የሚታይ ቤት አለበት፡፡ ተጠሪ የአርሶአደር ይዞታዎችን በተመለከተ የይዞታ ማረጋገጫ አገልግሎት አሰጣጥን አስመልክቶ ባወጣው መመሪያ ቁጥር 20/2013 መሰረት በይዞታው ላይ አገልግሎት ለማግኘት በመጠባበቅ ላይ ባለሁበት ወቅት አመልካች ይዞታዬን ለግሪን ኤርያ አገልግሎት የሚውል መሆኑን በፕላን በማያመለክትበት መኪያ ከድር ለምትባል ግለሰብ በግሪን ኤርያነት እንድትጠቀም በ27/6/12ዓ.ም ሰጥቷል፡፡ ስለሆነም አመልካች ይዞታዬን በመንጠቅ ለ3ኛ ወገን አስተላልፎ የሰጠበት በ27/6/12ዓ.ም የፈጸመው ውል እንዲሰረዝ፤ የተሰጣቸው ግለሰቦች ይዞታዬን ለቀው ይዞታዬን እንዲመልስ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ ማስረጃዎችንም አቅርበዋል፡፡ጥሩ የንባብ ጊዜ…