Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • President Message
    • President
      • Current President
      • Former President
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • History and Traditions
    • Judges
      • Former Judges
    • Vision Mission and Mandate
    • Judicial Administration Council
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
    • NEWS
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Tender
  • Judgement Execution Directorate
    • About Judgement Execution Directorate
    • Auction
  • Vacancy
  • Child Justice Project

ጠቋሬ ፈለቀ እና አባ ምትኩ ዘዉዴ የሰ.መ.ቁ.253916

Wednesday, June 4, 2025 4910

ይህ የአፈጻጸም ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል በዳህና ወረዳ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁን አመልካች የሥር ፍርድ ባለመብት፣ የአሁን ተጠሪ የሥር የፍርድ ባለዕዳ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር፡፡ ጉዳዩ ለዚህ ሰበር ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ አመልካች የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ.0337693 ሰኔ 15 ቀን 2015 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልኝ በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ፡፡

የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ በግራ ቀኛዉ መካከል በነበረዉ የይዞታ ክርክር የሥር የወረዳዉ ፍ/ቤት የአሁን ተጠሪ ለክርክር መነሻ የሆነዉን ይዞታ ለቆ ለአመልካች እንዲያስረክብ መወሰኑን መዝገቡ ያሳያል፡፡ የአሁን አመልካች ፍርዱን ለማስፈጸም የአፈጻጸም አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን የወረዳዉ ፍ/ቤቱ የአሁን አመልካች በይዞታዉ ላይ ባለመብት ከመሆኑ በፊት የአሁን ተጠሪ በይዞታዉ ላይ ሁለት ክፍል ያለዉን ቤት መስራቱን በማረጋገጥ አመልካች የቤቱን ግምት ለተጠሪ እንዲከፍልና ተጠሪ ይዞታዉን ለቆ ለአመልካች እንዲያስረክብ ብይን መስጠቱን የዉሳኔዉ ግልባጭ ያመለክታል፡፡ በየደረጃዉ ያሉት የክልሉ ፍ/ቤቶችም የቀረበላቸዉን ቅሬታ ዉድቅ በማድረግ የሥር ፍ/ቤትን ዉሳኔ በማጽናት መወሰናቸዉን የሥር ፍ/ቤት የዉሳኔ ግልባጭ ያሳያል፡፡ የአሁን የሰበር አቤቱታ የቀረበዉ በዚህ ዉሳኔ ቅር በመሰኘት ለማስለወጥ ነዉ፡፡

የአሁን አመልካች መስከረም 4 ቀን 2016 ዓ.ም በተጻፈ የሰበር አቤቱታ፡ የአሁን ተጠሪ በዋናዉ ጉዳይ ላይ ተከራክሮ የቤት ግምት ካሳ እንዲከፈለዉ የፍርድ ባለመብት ባልሆነበት የሥር ፍ/ቤት በዋናዉ ፍርድ የቤት ግምት ካሳ ጉዳይ ለተጠሪ እንዲከፈል ባልተወሰነበት፣ ተጠሪ በይዞታዉ ላይ በሕገወጥ መንገድ ቤቱን ሲሰራ አመልካች እየተቃወምኩት መሆኑን ተረጋግጦ ባለበት የሥር ፍ/ቤት በዋናዉ ፍርድ መሰረት ለክርክር መነሻ የሆነዉን 10 በ15 ካ.ሜ የሆነዉን ይዞታ ተጠሪ ለአመልካች እንዲለቅ ማስፈጸም ሲገባዉ አመልካች ለተጠሪ የቤቱን ግምት እንዲከፍል መወሰኑ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ እንዲታረምልኝ በማለት በዝርዝር አመልክቷል፡፡መልካም ንባብ….

Read more

እስጢፋኖስ /ዩቡና/ ዲራጎ እና የሲዳማ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የሠ/መ/ቁጥር 251519

Wednesday, June 4, 2025 4948

አመልካች በቀን 26/11/2015ዓ/ም የተጻፈ የሰበር አቤቱታ የቀረበውም የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት መጽናቱ መሰረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለት ሲሆን ይዘቱ በአጭሩ - አመልካች ድርጊቱ በተፈጸመበት ቦታ ነበርኩኝ እንጂ ድርጊቱን አልፈጸምኩም፤ የተጠሪ ምስክሮች ድርጊቱን ስለመፈጸሜ አላስረዱብኝም፤ ባቀረብኩት ምስክር ወንጀሉን ያልፈጸምኩ መሆኑን አስረድቻለሁ፤የተጠሪ ምስክሮች እርሱን ይመስላል ከማለት ውጪ ድርጊቱን ስለመፈጸሜ አላስረዱም፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የስር ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠዉን ዉሳኔ በማጽናት የወሰነዉ በወንጀል ሕግ አንቀጽ 23/2 ስር በተደነገገዉ መሠረት የግድያ ወንጀል መፈጸሜ ሳይረጋገጥ በመሆኑ ዉሳኔዉ ከዚህ ድንጋጌ አፈጻጸም ጋር በተያያዘ በሰ/መ/ቁጥር 22069 ስር የተሰጠዉን አስገዳጅ የሕግ ትርጉም የሚቃረን ነዉ፡፡ስለሆነም ተጠሪ ያቀረባቸው ምስክሮች አመልካች ድርጊቱን ስለመፈጸሜ ከጥርጣሬ በላይ ያላስረዱ ስለሆነ የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠው የጥፋተኝነት እና የቅጣት ውሳኔ ተሽሮ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት የሰጠው ውሳኔ እንዲጸናል፡፡የክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት የሰጠዉ የጥፋተኝነት ውሳኔው የሚያጸና ከሆነም አንቀጹ ወደ ወንጀል ሕግ አንቀጽ 540 እንዲቀየርልኝ እና የ3ኛ አመት የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ስለሆንኩ ቅጣቱ በወ/ህ/አንቀጽ 192 መሰረት እንዲገደብልኝ በማለት አመልክቷል፡፡መልካም ንባብ….

Read more

የየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ቀበሌ 11/12/08 ሸማቾች ኃ/የተ/ሕ/ሥ/ማ እና አቶ እንኮሳ አመንቴ ሱፋ(9ሰዎች)የሰ.መ.ቁ 249104

Wednesday, June 4, 2025 4682

የክሱ ይዘት በአጭሩ፡- በየካ አውራጃ ከፍተኛ 16 ቀበሌ 08 የቀድሞው የቀበሌ አመራሮች የተጠሪዎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመቅረፍ በማሰብ ከህብረት ሥራ ማህበር ብር 29.000 (ሃያ ዘጠኝ ሺህ ብር) በብድር መልክ ወጪ ተደርጎ ቤት እንድንገነባ ተፈቅዶልን ቤቶቹን በመገንባት የብድር ገንዘብም  ተመልሷል፤ ተጠሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ነዋሪዎች በራሳችን ገንዘብ ቤቶቹን አፍርሰን እንደሰራን በወቅቱ የነበሩ የአመልካች አመራሮች አረጋግጠው በሰነድ ማስረጃ ሰጥተውናል፤ ተጠሪዎች ከ1982/1983 ጀምሮ በሰነድ አልባ በመኖሪያ ቤቶቹን ገንብተን እየኖርን እያለን ከ20 ዓመታት በኋላ አመልካች ለተጠሪዎች ያሰበ በማስመሰል ከፊሎቹን የተጠሪዎች ቤቶች ለልማት ሊፈርሱ ስለሚችሉ የጋራ መኖሪያ ቤት መንግስት እንዲሰጣችሁ እና ቀበሌው እንዲያውቃችሁ በማለት ከሱ ጋር የቤት ኪራይ ውል እንድንዋዋል ሲጠይቀን ተጠሪዎችም የአመልካች ህብረት ሥራ ማህበር አባላት በመሆናቸን እና መንግስታዊ ተቋም ነው ብለን በማመን ከ2ኛ ተጠሪ በስተቀር ከአመልካች ጋር የቤት ኪራይ ውል ልንፈርም ችለናል፤ተጠሪዎች የይዞታ ማረጋገጫ ለመቀበል በሂደት ላይ እያለን አመልካች ከህግም ሆነ ከውል የመነጨ መብት ሳይኖረው እንዳይፈጸም አድርጓል፤ አመልካች ተጠሪዎችን በማታለል ባስፈረመን የኪራይ ውል መነሻነት ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ኪራዩን ከፍለው ቤቱን ያስረክቡኝ በማለት ክስ አቅርቦ ተጠሪዎች ቤቱን እንድናስረክብ ተወስኗል፤ ሆኖም ከመነሻው ቦታው በጎርፍ ምክንያት ለህይወታችን እስጊ በመሆኑ ልዋጭ ቦታ እንዲሰጠን የሚመለከተውን አካል ጠይቀን ሲሰጠን በቦታው ላይ ቀበሌው ቤት መስራት ካልቻለ ነዋሪዎች በራሳችን ወጪ እንድንሰራ በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በራሳችን ወጪ ቤት ገንብተን በስማችን ውሃ፣ መብራት እና መሰል መሰረታዊ አገልግሎቶችን አስገብተን የምንኖርበት ቤት በመሆኑ ቤቶቹ የተጠሪዎች ናቸው ተብሎ ይወሰንልን በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡መልካም ንባብ….

Read more

አቶ ታዬ ከተማ ደጋጋ እናእነ አቶ ሙሉጌታ ታደሰ (3ሰዎች) የሰ/መ/ቁጥር---244417

Wednesday, June 4, 2025 4717

ለዚህ ሰበር ክርክር መነሻ የሆነው የገጠር መሬት ይዞታ ዉርስን የተመለከተ ጉዳይ ሲሆን የተጀመረው በሲናና ወረዳ ፍ/ቤት ነው፡፡ በዚህ ፍ/ቤት 2ኛ ተጠሪ ከሳሽ፤ አመልካች ተከሳሽ ሲሆኑ 1ኛ እና 3ኛ ተጠሪዎች እንዲሁም አቶ ጉደታ ሸለማ እና አቶ መርጋ ደበላ ጣልቃ ገቦች ነበሩ፡፡ የሰበር አቤቱታዉ የቀረበዉ የባሌ ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ/ቁ 33516 መጋቢት 14 ቀን 2014 ዓ.ም የወረዳዉን ፍ/ቤት በማሻሻል የሰጠዉና በየደረጃዉ ባሉት የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ችሎቶች በተሰጡ ዉሳኔዎች የጸናዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በሚል ነዉ፡፡መልካም ንባብ…

Read more

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን እና ብርሃን ባንክ አክስዮን ማህበር ሰበር መዝገብ ቁጥር-242024

Friday, May 30, 2025 1837

ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ አመልካች በተጠሪ ላይ በስር ፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ ፍሬ ቃሉ በአጭሩ በከሳሽና በተክለ ብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ መካከል የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ውል መዋዋላቸውን ጥር 08 ቀን 2014 አ.ም ሰርቶ እንዲያጠናቅቅ መስማማታቸውን ነገር ግን ስራውን በውሉ መሰረት ባለመስራቱ ከሳሽ ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ የስራ ውሉን ያቋረጠ መሆኑን ለተቋራጩ ቅድመ ክፍያ በሁለት ዙር 96,000.00 እና 43,600,173.83 የተከፈለ መሆኑን ተከሳሽ ለቅድመ ክፍያ ዋስትና ብር 89,609,174.04 ለ 2 ዓመት ከ 5 ወር የሚቆይ ዋስትና የሰጠ መሆኑን ተከሳሽ የሰጠው የዋስትና አይነት ጥያቄ እንዳቀርብ የሚከፈል በመሆኑ ተከሳሽ የቅድመ ዋስትና ገንዘብ ብር 89,609,174.02 ከመስከረም 19 ቀን 2012 አ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ህጋዊ ወለድ ጋር እንዲከፍል የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…

Read more
FirstPrevious567891011121314NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions