23
ጉዳዩ እንዲህ ነው፡፡ ግራ ቀኙ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ/ቁ/179218 ላይ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 08 የቤ/ቁጥር 788 በሆነው ቤት ላይ ሲያደርጉት የነበረውን ክርክር አስመልክቶ የካቲት 25/2013 ዓ.ም የተደረገ የእርቅ ስምምነት በማቅረባቸው ፍርድ ቤቱም ስምምነቱን መርምሮ ከመዘገበ በኋላ መዝገቡን ዘግቶ ግራ ቀኙን አሰናብቷል፡፡
ይህ ከሆነ በኋላ የአሁን አመልካች ነሓሴ 25/2013 ዓ.ም በተፃፈ አቤቱታ የዳግም ዳኝነት ይታይልኝ አቤቱታ ለፍርድ ቤቱ ያቀርባሉ፡፡ ለአቤቱታቸው መሰረት የሆነውም ቀደም ሲል በመዝገቡ ላይ ክርክር ሲደረግበት የነበረውን ቤት አስመልክቶ የቤቱ ባለቤት አቶ ይልማ ይፍሩ ጥር 07/2000 ዓ.ም ባደረጉት ኑዛዜ ወ/ሪት ራሄል ይልማ የተባለችዋን ልጃቸውን የኑዛዜው ተጠቃሚ አድርገው የአሁን አመልካችን ደግሞ የኑዛዜው ጠባቂ ያደረጓቸው መሆኑን፤ ቀደም ሲል ይህነኑ ቤት አስመልክቶ ከአሁን ተጠሪ ጋር በፍርድ ቤቱ ሲከራከሩ የነበሩትም በዚሁ ኑዛዜ ጠባቂነታቸው ችሎታ መሆኑን፤ በፍርድ ቤት የነበረው ክርክር በእርቅ ከመጠናቀቁ በፊት የአሁን ተጠሪ በወ/ሪት ራሄል ይልማ ላይ የመጥፋት ውሳኔ ማሰጠታቸውን ከእርቅ ስምምነቱ በኋላ ያወቁ መሆኑን፤ የመጥፋት ውሳኔ መኖሩን ቀድመው ቢያውቁ ኖሮ የእርቅ ስምምነቱን እንደማይፈርሙ እና ፍ/ቤቱም ስምምነቱን እንደማይመዘግብ ጠቅሰው የእርቅ ስምምነቱ ውድቅ ተደርጎ ወደነበሩበት እንዲመለሱ የሚጠይቅ ነው፡፡...
23
ተጠሪ ባቀረቡት አቤቱታ ከአሁን አመልካች ጋር በቀን 20/2/2012 ዓ/ም በተደረገ የኢንሹራንስ ውል የተጠሪ ንብረት በሆነው በሰሌዳ ቁጥር 3-66921 ኦሮ የተመዘገበ ተሸከርካሪ ላይ በአደጋ ምክንያት ለሚደርስ ጉዳት ሽፋን ተሰጥቷል፤ ተጠሪ በቀን 6/3/2012 ከአዲስ አበባ ወደ ቢሾፍቱ ከተማ መኪናውን እያሽከረከሩ በነበረበት ወቅት በዱከም ከተማ ማልካ ዱከም ቀበሌ ላይ በቸልተኛነት በደረሰ አደጋ በተሸከርካሪው እና በሰዎች ላይ ጉዳት ደርሷል፤ አመልካች በመድን ውሉ መሰረት የተጎዳውን የተጠሪ ተሸከርካሪ በወቅቱ አስጠግኖ መስጠት ሲገባው ሳያስጠግን በመቅረቱ ከአደጋው ጊዜ ጀምሮ ተሸከርካሪው ያለስራ ቆሟል፤ አመልካች በ22/04/2012 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ (የፕሮፎርማ ማስታወቂያ) ተሸከርካሪውን ለማሰራት የሚያስፈልጉ መለዋወጫዎች ዋጋ እንዲቀርብ ጠይቆ ፕሮፎርማ ተሰብስቦ ቢቀርብም አመልካች ነገ ዛሬ እያለ ሳያስጠግን ቀርቷል፤ ስለሆነም ተሸከርካሪው ቢያንስ በቀን 500.00 ብር የተጣራ ገቢ የሚያስገኝ ሲሆን ሳይጠገን ለአንድ አመት ከሰባት ወር በመቆሙ ክሱ እስከቀረበበት ጊዜ ድረስ ያለውን ከሳሽ ማግኘት ያለበት የአንድ አመት ገቢ ተሰልቶ ብር 180000.00 እና የተሸከርካሪው ማስጠገኛ ወጪ ብር 350000.00 በአጠቃላይ ብር 530000.00 (አምስት መቶ ሰላሳ ሺህ) ከልዩ ልዩ ወጪዎች ጋር የአሁን አመልካች እንዲከፍል እንዲወሰን በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡...
21
የክሱ ይዘት በአጭሩ የሟች ወላጅ አባታችን እና እናታችን የማይንቀሳቀሱ እና የሚንቀሳቀሱ ንብረቶች የሆኑትን 1ኛ በሐረሪ ከልል ድሬ ጠያራ ወረዳ አቦከር ሙጢ ቀበሌ ልዩ ስሙ ገንደ አመሬሃሮ በሚባል ቦታ የሚገኝ ጠቅላላ ስፋቱ 8 ጥማድ፤ 2ኛ በድሬ ጠያራ ወረዳ አቦከር ሙጢ ቀበሌ ልዩ ስሙ ገንደ አሊሾ ቦቄፈራ ተብሎ በሚጠራ ስፍራ የሚገኘውን 16 ጥማድ፤ 3ኛ በአቦከር ሙጢ ቀበሌ ልዩ ስሙ መቆራ ገንደ ሃሰይ በሚባል አከባቢ የሚገኝ ስፋቱ አምስት ጥማድ የሆነውን ይዞታ፤ 4ኛ በተመሳሳይ በገዳ ሃሰይ የሚገኝ 4 ጥማድ የእርሻ ይዞታ፤ 5ኛ በድሬ ጠያራ ወረዳ በአቦከር ሙጢ ቀበሌ ልዩ ስሙ አቦከር ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የሚገኘውን የጫት ተክል ግምቱ ብር 10,000 የሆነ፤ 6ኛ በጥሬ ጠየራ ወረዳ በአቦከር ሙጢ ቀበሌ የሚገኘውን የወላጅ አባታችን 100 ቆርቆሮ ቤት ግምቱ ብር 30,000 የሚያወጣ፤ 7ኛ በሐረሪ ክልል ቀላድ አምባ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የሚገኘውን ባለ 30 ቆርቆሮ ቤት ግምቱ 20,000 የሆነውን ተጠሪ እና የስር 2ኛ ተከሳሽ ለብቻቸው ይዘው እየተጠቀሙበት በመሆኑ በይዞታው ላይ ለሚደርሰው ጉዳት ሃላፊ ናቸው ይባልልን፤ግራ ቀኛችን በምንመርጣቸው ሽማግሌዎች እንድንከፋፈል እንዲሁም ቤቶቹ ተገምተው ካልተስማማን በሀራጅ እንዲሸጥ እና ከሳሾች በይዞታው ላይ ለቀየሩትና ለተከሉት ተክሎች ካሳ መጠየቅ አትችሉም ይባልልን በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ ...
22
አመልካች በጥር 15 ቀን 2013 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት ክስ በሲዝ ከተማ ቀበሌ 01 ክልል ውስጥ ሰላም ሰፈር በሚባል አከባቢ የሚገኝ ቦታ የአባታችን የውርስ ሀብት ሆኖ እያለ ተጠሪዎች ለራሳቸው ብቻ እየተጠቀሙ ስለለሚገኙ እና እኔ ህጋዊ ወራሽነቴን ስላረጋገጥኩ ድርሻዬን እንዲያካፍሉ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ ....
28
የአቤቱታው ይዘትም በአጭሩ፦ የተጠሪዎች ወላጅ አባት አቶ ጸጋዬ ገ/ሚካኤል ታህሳስ 23 ቀን 2000ዓ.ም ከዚህ አለም በሞት የተለዩ እና ኑዛዜም ያልተው መሆናቸውን እንዲሁም ተጠሪዎች የመጀመሪያ ደረጃ ወራሾች መሆናቸው ተረጋግጦ በፌ/የመ/ደ/ፍ/ቤት ንፋስ ስልክ ላፍቶ 1ኛ ፍ/ብሔር ችሎት በመ/ቁ 108551 የሟች የውርስ ሀብት ሪፖርት የማጽደቅ ውሳኔ የተሰጠላቸው መሆኑን ገልጸው ሟች በን/ላ/ክ/ከተማ ወረዳ 02 ከዚህ በተባለ የጋራ ህንጻ መኖሪያ ቤት ኃ/የተ/የሕ/ሥ/ማህበር መስራች አባል በመሆን በስማቸው ተመዝግቦ የሚታዎቅና የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ያልወጣለት 94 ካ.ሜ ስፋት ያለውን ጅምር ቤታቸውን 1ኛ ተከሳሽ ከእኛ እውቅና ውጭ በሌላ ሰው መተካቱ ተገቢ ባለመሆኑ፤ 2ኛ ተከሳሽ ወራሾች ስለመሆናችን አረጋግጠን በስማችን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ እንዲሰጠን ስንጠይቅ ፍቃደኛ ባለመሆኑና ሟች ከሞተ ከ3 አመት በኋላ ሟች የሰጠውን ውክልና መሰረት በማድረግ የፈጸመው መተካካት ተገቢ ባለመሆኑ፤3ኛ ተከሳሽ ለ4ኛ ተከሳሽ መተካካቱን የፈጸመው በሞተ ሰው ውክልና በመሆኑና ማጣራት ያለበትን ተግባር ያላጣራ በመሆኑ እንዲሁም 4ኛ ተከሳሽ የሟች አባታችንን ይዞታ የያዘበት አግባብ ተገቢነት የሌለው በመሆኑ እኛ ህጋዊ ወራሾች ተተኪ ተደርገን እንደንመዘገብ ይወሰንልን በሚል የቀረበ ነው፡፡ ......