ጉዳዩ የተጀመረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሲሆን አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ አመልካች በተጠሪ ላይ በስር ፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ ፍሬ ቃሉ በአጭሩ በከሳሽና በተክለ ብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማ መካከል የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ውል መዋዋላቸውን ጥር 08 ቀን 2014 አ.ም ሰርቶ እንዲያጠናቅቅ መስማማታቸውን ነገር ግን ስራውን በውሉ መሰረት ባለመስራቱ ከሳሽ ማስጠንቀቂያ ሰጥቶ የስራ ውሉን ያቋረጠ መሆኑን ለተቋራጩ ቅድመ ክፍያ በሁለት ዙር 96,000.00 እና 43,600,173.83 የተከፈለ መሆኑን ተከሳሽ ለቅድመ ክፍያ ዋስትና ብር 89,609,174.04 ለ 2 ዓመት ከ 5 ወር የሚቆይ ዋስትና የሰጠ መሆኑን ተከሳሽ የሰጠው የዋስትና አይነት ጥያቄ እንዳቀርብ የሚከፈል በመሆኑ ተከሳሽ የቅድመ ዋስትና ገንዘብ ብር 89,609,174.02 ከመስከረም 19 ቀን 2012 አ.ም ጀምሮ ከሚታሰብ ህጋዊ ወለድ ጋር እንዲከፍል የሚል ነው፡፡መልካም ንባብ…