ይህ የእርሻ መሬት ክርክር የተጀመረዉ በየም ልዩ ወረዳ ፍ/ቤት ሲሆን፣ የአሁን አመልካች የሥር ከሳሽ፣ የአሁን ተጠሪ የሥር ተከሳሽ ሆኖ ሲከራከሩ ነበር። ጉዳዩ ለዚህ ችሎት ሊቀርብ የቻለዉ የአሁን አመልካች የደቡብ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ.14976 በ1/9/2012 ዓ.ም የሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ስለሆነ እንዲታረምልን በማለት በማመልከታቸዉ ነዉ።
የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ የአሁን አመልካች በሥር ፍ/ቤት ባቀረበዉ ክስ በሟች አባቴ አቶ አባገላን አባጊቤ እጅ ለ56 ዓመታት የቆየን ባህር ዛፍ ይዞታ ከዚህ ቀደም በመ.ቁ.09921 ላይ ባህር ዛፍ የሟች አባቴ ነዉ ተብሎ የተወሰነዉ የዉርስ ይዞታዬን በጉልበት ስለያዘብኝ የአሁን ተጠሪ ይዞታዉን እንዲለቅልኝ፣ የወደመዉን ንብረት ግምትና በክሱ ምክንያት የወጠዉን ወጪና ኪሳራ የመጠየቅ መብት እንዲጠበቅልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡……………..