Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • President Message
    • President
      • Current President
      • Former President
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • History and Traditions
    • Judges
      • Former Judges
    • Vision Mission and Mandate
    • Judicial Administration Council
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Tender
  • Judgement Execution Directorate
    • About Judgement Execution Directorate
    • Auction
  • Vacancy
  • Child Justice Project

እነ ቤተልሄም ጌቱ አለሙ እና የፌ/ጠ/ ዐቃቤ ህግ የሰ.መ.ቁ. 203654

Friday, February 25, 2022 13807

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካቾች የካቲት 30 ቀን 2013 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ በሐረሪ ህዝብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት መ.ቁ. 05450 የካቲት 01 ቀን 2013 ዓ.ም የሰጠውን ብይን፤ በማጽናት የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት መ.ቁ. 00159 የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም የሰጠው ትዕዛዝ መሠረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረባቸው ነው፡፡

ጉዳዩ የወንጀል ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በሐረሪ ህዝብ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው፡፡ የአሁን ተጠሪ በአሁን አመልካቾች ላይ በስር ፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ ይዘት በአጭሩ፡-  የሙስና ወንጀል አዋጅ ቁጥር 881/2007  አንቀጽ 31(1) እና (2)  በመተላለፍ አመልካቾች የእምነት ማጉደል ወንጀል ፈጽመዋል የሚል ነው፡፡ የአሁን አመልካቾች ክሱን በሚመለከት ያቀረቡት መቃወሚያ በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ህገ መንግስት አንቀጽ 78(2)፤ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ማደራጀ አዋጅ ቁጥር 322/96 አንቀጽ 2 እና በአዋጅ ቁጥር 434/97 መሰረት ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለማየት ስልጣን የለውም፤ አመልካቾች እምነት አጉድለዋል የተባለበት የግል የጤና አገልግሎት ከሚሰጥ ድርጀት ጋር በተያያዘ እንጂ የመንግስት መስሪያ ቤት ወይም የመንግስት የልማት ድርጅት ባለመሆኑ በአዋጅ ቁጥር 881/2007 ስር ክስ ሊቀርብ አይገባም በማለት ከክሱ በነፃ እንዲሰናበቱ ጠይቀዋል፡፡………

Read more

ብሩክ አስፋው እና የፌደራል ጠቅላይ ዐ/ሕግ የሰ/መ/ቁጥር 203603

Thursday, February 24, 2022 15496

ጉዳዩ አመልካች በኢትዮጵያ የፖሊስ ሰራዊት ላይ እንዳይፈፀም የተከለከለን ድርጊት በመፈፀሙ የወንጀል ክስ ቀርቦበት ጥፋተኛ ተብሎ በእስራት እንዲቀጣ ከተወሰነበት በኋላ የይግባኝ አቤቱታ ማቅረቢያ ጊዜው ስላለፈበት  ይግባኙን ጊዜው ካለፈ በኋላ እንዲያቀርብ እንዲፈቀድለት ለከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ያቀረበ ቢሆንም የማቅረቢያ ጊዜው ያለፈውን ይግባኝ ለመቅረብ የሚያስችል በቂ ምክንያት አልቀረበም ተብሎ ውድቅ መደረጉ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ነው ተብሎ እንዲታረምለት ያቀረበውን የሰበር አቤቱታ የሚመለከት ነው፡፡………..

Read more

አቶ ገመቹ ቤኩማ እና የሔና ፋርም ኃ/የተ/የግ/ማህበር ሰበር መ/ቁ/ 203210

Thursday, February 24, 2022 12640

ጉዳዩ አመልካች ያቀረበዉ ጊዜ ያለፈበት ይግባኝ ማስፈቀጃ ጥያቄ ተቀባይነት ባለማግኘቱ የቀረበ አቤቱታ የሚመለከት ነዉ፡፡ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ከሳሽ በመሆን የአሁኑ ተጠሪ ላይ ባቀረበው ክስ በተጠሪ ሆቴል ውስጥ ተቀጥሬ እየሰራሁ እያለ ያለጥፋት የስራ ውል ስለአቋረጠብኝ የስራ ስንብት ክፍያዎች እንዲከፈለኝ በማለት ዳኝነት የጠየቀ ሲሆን ተጠሪ በሰጠዉ መልስ አመልካችን አላሰናበትንም ይልቁንም አመልካች ካለበት ዕዳ ለመሸሽ ሲል ስራውን ለቆ በመሄዱ ተጠሪ ላይ ጉዳት ደርሷል በማለት ተከራክረዋል፡፡…….

Read more

ወ/ሮ ዲዮን ማክፋርላን እና ላየን ኸርት አካዳሚ ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሰ/መ/ቁ. 202879

Thursday, February 24, 2022 11725

ጉዳዩ የስራ ስንብትን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረውም በፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በስር ፍርድ ቤት በነበረው ክርክር አመልካች ከሳሽ፣ ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ በመሆን የተከራከሩ ሲሆን አመልካች በቀን 07/01/2012 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት ክስ ተጠሪ እኔ ባለሁበት የስራ መደብ ላይ በተመሳሳይ ለሚሰሩ ሰራተኞች የሐምሌ እና የነሐሴ ደሞዝ ሲከፍል ለእኔ ግን የሚገባኝ ክፍያ ባለመክፈል በፈፀመው ህገ-ወጥ ተግባር ሞራሌ የተነካ በመሆኑ ያልተከፈለኝን የሁለት ወር ደሞዝ፣ የስራ ስንብት ክፍያ ፣ ካሳ፣ ክፍያ በተገቢው ጊዜ ውስጥ ባለመክፈሉ ቅጣት እና የዓመት እረፍት ክፍያ እንዲከፍል ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀው ተከራክረዋል፡፡…………..

Read more

እነ ወ/ሮ ከበቡሽ ቡሎየ እና አቶ መንግሥቱ ባለህ ሰ/መ/ቁ. 202681

Thursday, February 24, 2022 11785

የሰበር አቤቱታው የቀረበው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው አመልካቾች የስር ከሳሾች ሲሆኑ ተጠሪ ተከሳሽ ነበሩ፡፡ አመልካቾች ያቀረቡት ክስ በተጠሪ የንግድ ሥራ በልብስ ስፌት፣ በልብስ እጅ ሥራና ዝምዘማ የሥራ መደብ ተቀጥረን ስንሰራ ነሀሴ 28 ቀን 2011 ዓ/ም ከሕግ ውጭ በቃል ከሥራ አሰናብቶናል፡፡ የሥራ ስንብቱ ሕገ-ወጥ ስለሆነ የአገልግሎት ክፍያ፣ ካሣ፣ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ክፍያ፣ የዓመት ዕረፍት፣ ትርፍ ሰዓት የተሰራበት ክፍያ እንዲሁም ክፍያው ለዘገየበት ቅጣት እንዲከፈላቸው እና የሥራ ልምድ እንዲሰጣቸው ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡………..

Read more
Previous12345678910NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions