25
በስር ፍርድ ቤት አመልካች በተጠሪ ላይ መጋቢት 15 ቀን 2013 ዓም በተጻፈ በመሰረቱት ክስ ተጠሪ በአዲስ አበባ ከተማ በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ስሙ ድጋፌ ሰፈር አካባቢ ኮንስትራክሽን ስራ የተሰማሩና ባለቤት ናቸው፡፡ ተጠሪ በድርጅታቸው ግቢ ውስጥ በርካታ ውሾች አሏቸው ተጠሪ በባለቤትነት የያዟቸውን ውሾች በአግባቡ መያዝና መጠበቅ ሲገባቸው ከጊቢ ውጪ በመልቀቃቸው አመልካች በብድር ብር የማረባቸውን ዶሮዎች በቁጥር 127 የሚሆኑትን በውሾቻቸው እንዲበሉ በማድረጋቸው ኪሳራ ደርሶብኛል፡፡ ተጠሪ ቀደም ሲልም 2 በጎችን አስበልተውብኝ ውሾቹን እንዲጠብቁ ቢነገራቸውም ሌላ ኪሳራ እንዲደርስብኝ አድርገዋል፡፡ በመሆኑም ተጠሪ ተገቢውን ጥበቃ ማድረግ ሲገባቸው በውሾቻቸው የተበሉትን 127 ዶሮዎች ግምት ብር 63,500(ስልሳ ሶስት ሽህ አምስት መቶ ብር) በዚህ ምክንያት ለወጣው ወጪና ኪሳራ ጭምር እንዲከፍሉኝ እንዲወሰንለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡
ጥሩ ንባብ…
18
ጉዳዩ ካሣን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍ/ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን ተጠሪ ከሳሽ፤ የአሁን አመልካች 1ኛ ተከሳሽ፤ በዚህ የሰበር ክርክር የሌለው የኦሮሚያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ደግሞ 2ኛ ተከሳሽ ነበሩ፡፡ የአሁን ተጠሪ በሥር ፍ/ቤት ያቀረቡት ክስ ይዘት በአጭሩ፡- በ1996 ዓ.ም በኢንቨስትመንት በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ጃርደጋ ጃርቴ ወረዳ ከጃሪ ስሬ ቀበሌ ውስጥ ለግብርና ልማት የሚውል 250 ሔክታር መሬት ተሰጥቶኝ ሳለማ ቆይቻለሁ፤ ከዚሁ ይዞታ ውስጥ 90 ሔክታር በአመርቲ ነሺ መብራት ሀይል ካሳው ተገምቶ ተወስዷል፤ ቀሪው 160 ሔክታር ፊንጭአ ስኳር ፋብሪካ ሸንኮራ ሊያመርትበት ወስዶታል፤ በዚሁ መሬት ላይ የተለያዩ ሰብሎችን በማምረት ያደረግኩት ማሻሻያ ተገምቶ ሊከፈለኝ ሲገባ ከመሬቴ ላይ አፈናቅሎኛል፤ ከመሬቱ ማግኘት የሚገባኝንም ጥቅም እና ገቢ አሳጥቶኛል፤ ስለሆነም በቦታው ለይ ያመረትኳቸው የተለያዩ ሰብሎች ግምት እና ለመንገድ ስራ ያወጣሁት ወጪ በድምሩ ብር 29,002,828.80 አመልካች እንዲከፍለኝ፤ የስር 2ኛ ተከሳሽ ደግሞ መሬቱን እንዳለማሁ እና አመልካች እንደወሰደው እያወቀ በውላችን አንቀጽ 6 ላይ የገባውን የዋስትና ግዴታ በመተው ያለካሳ እና ያለአንድም ምትክ መሬት እንድለቅ ያደረገ በመሆኑ ከአመልካች ጋር ተጠያቂ ነው ተብሎ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡ጥሩ ንባብ…
28
የክርክሩ ሥረ ነገር አመጣጥ እንዱህ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሰኔ 2013 ዓ.ም ከተዯረገው 6ኛው ሀገር አቀፌ ምርጫ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ዜጎች ሇማህበራዊ ፌትህ(ኢ.ዜ.ማ) በዯቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ብሔራዊ ክሌሌሊዊ መንግስት ከተዯረጉት ምርጫዎች ውስጥ የምርጫ አዋጁን እና አዋጁን ሇማስፇፀም የወጡትን ዯንቦች እና መመሪያዎችን ባሌተከተሇ መሌኩ ምርጫው ተከናውኖባቸዋሌ ያሊቸውን የምርጫ ክሌልች ሇይቶ ውዴቅ እንዱዯረግሇት በአሁን ተጠሪ ሊይ በፋዳራሌ ጠቅሊይ ፌርዴ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችልት በመ/ቁ/211141 ሊይ ይግባኝ አቅርቧሌ፡፡ ይግባኙ ከቀረበባቸው የምርጫ ክሌልች ውስጥ አንደ የጋሞ ዞን የቁጫ ምርጫ ክሌሌ ነው፡፡ ፌርዴ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር እና ማስረጃን ከሰማ በኋሊ ነሓሴ 21/2013 ዓ.ም በዋሇው ችልት የቁጫ ምርጫ ክሌሌን ጨምሮ የአራት የምርጫ ክሌልች ውጤትን በመሰረዝ ተጠሪ በእነዚህ የምርጫ ክሌልች ሊይ ዴጋሚ ምርጫ እንዱያካሂዴ ወስኗሌ፡፡ጥሩ ንባብ….
13
ይዘቱም ባጭሩ፡በአመልካች ድርጅት ተቀጥረዉ በማገልገል ላይ እያሉ መንግስት ከሕዳር ወር ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በወሰደዉ እርምጃ የአመልካች ድርጅት ከሥራ በማገድ ሠራተኞች በሥራ ላይ እንዲቆዩና ደመወዝ እንዲከፈላቸዉ በሰጠዉ መመሪያ መሠረት ሲሠራ በነበረበት ቦታ ላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን መንግስት በወሰደዉ እርምጃ የአመልካች ድርጅት የስራ ፈቃድ በመሠረዙና የሥራ ዉሉ በመቋረጡ መንግስት ለሰራተኞች ከስንብት ጋር ተያያዥነት ያላቸዉን ክፍያዎች እና መብቶችን እንዲጠብቅላቸዉ በወሰነዉ መሰረት የስራ ስንብት፣ የማስጠንቀቂያ ጊዜ፣ ክፍያ የዘገየበት እና ያልተጠቀሙበት የዓመት እረፍት በደመወዛቸዉ ልክ ታስቦ ለእያንዳንዳቸዉ እንዲከፈላቸዉ እንዲሁም የስራ ልምድ ምስክር ወረቀት እንዲሰጣቸዉ እንዲወሰን በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ጥሩ የንባብ ጊዜ፡፡
32.ስብሐቱና ልጆቹ የንብረት አስተዳደርና የጥበቃ አገልግሎት እና እነ አቶ ጌታቸዉ ደመቀ ጣሰዉ የሰ.መ.ቁ.236462
የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ ከሳሾች በሥር ፍ/ቤት ባቀረቡት ክስ፡- ከሳሾች በተከሳሽ ድርጅት በጥበቃ አገለግሎት ሥራ የተቀጠሩበትና ሲከፈላቸዉ የነበረዉን ደመወዝ በመጥቀስ መንግስት በወሰዳዉ እርምጃ ህዳር 4 ቀን 2013 ዓ.ም የተከሳሽን ድርጅት እንዲታገድ፣ የሥራ ፈቃድን በመሰረዝ እና ለዘለቄታዉ እንዲዘጋ የተደረገ በመሆኑ፣ የስራ ስንብት፣ የማስጠንቀቂያ ጊዜ እና ያልተጠቀምንበት የዓመት እረፍት፣ ክፍያ የዘገየበት ቅጣት እንዲከፈለን፣ የሥራ ልምድ ማስረጃ እንዲሰጠን በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡ ጥሩ ንባብ…
21
ጉዳዩ የስራ ክርክርን መሰረት ያደረገ ነዉ፡፡ክርክሩ የተጀመረዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ስሆን አመልካች ተከሳሽ ተጠሪዎች ከሳሾች በመሆን ተከራክረዋል፡፡ለሰበር አቤቱታ መነሻ የሆነዉ ጉዳይ የፌዴራል የመጀመሪ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 175479 ላይ በ06/10/2014 ዓም በዋለዉ ችሎት የሰጠዉ ፍርድ እና የፈዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 174576 ላይ በ09/02/2015 ዓም በማሻሻል የወሰነዉ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፅመበት ሰለሆነ በሰበር ታይቶ ይታረምልኝ በማለት አመልካች የሰበር አቡቱታ ጥቅምት 25 ቀን 2015 ዓም በተፃፈ በማቅረባቸዉ ነዉ፡፡ጥሩ ንባብ…