ዘሀራ ሰዒድ እና የደቡብ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ መዝገቡ ሰ-መ-ቁ 193294
የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም ጽፋ ባቀረበችው የሰበር አቤቱታ በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 31781 የካቲት 09 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት በስሩ ያሉት ፍርድ ቤቶች የሰጡትን የጥፋተኛነት እና የቅጣት ውሳኔ በማጽናት የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረቧ ነው፡፡
ጉዳዩ ወንጀልን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጂንካ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው፡፡ የአሁን ተጠሪ በአሁን አመልካች እና በስር 2ኛ ተከሳሸ ላይ በስር ፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ ይዘት በአጭሩ……..