Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • President Message
    • President
      • Current President
      • Former President
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • History and Traditions
    • Judges
      • Former Judges
    • Vision Mission and Mandate
    • Judicial Administration Council
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
    • NEWS
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Tender
  • Judgement Execution Directorate
    • About Judgement Execution Directorate
    • Auction
  • Vacancy
  • Child Justice Project

እነ አቶ ፈልመታ አምቦ እና ወ/ሮ ብርሃኔ ደምሴ የሰ-መ-ቁ 189090

Sunday, May 2, 2021 20115

ጉዳዩ በቤት ሽያጭ ውል መሰረት ቤቱን አስለቅቆ ለመረከበ ዳኝነት ተጠይቆ በቀረበ ክስ መነሻ የተሰጠዉ ዉሳኔ መሰረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል ተብሎ የቀረበ የሰበር አቤቱታ የሚመለከት ነዉ፡፡ ክርክሩ በተጀመረበት በፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአሁን አመልካች 2ኛ ተከሳሽ በመሆን የአሁን ተጠሪ ደግሞ ከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ ተጠሪ በአመልካች እና በስር 1ኛ ተከሳሽ ወ/ሮ ዛይድ መኮንን ላይ በመሰረቱት ክስ የስር 1ኛ ተከሳሽ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ በቀድሞ አጠራር ቀበሌ 02 ክልል ውስጥ በምስባክ የመኖሪያ ቤት ህብረት ስራ ማኅበር ስም በካርታ ቁጥር 62/96/1119/90 ተመዝግቦ በተሰጠው ቦታ በማኅበር ተደራጅተው ተሸንሽኖ  በተሰጣቸዉ የቦታ ቁጥር 99 በሆነ 175 ካ/ሜ ቦታ ላይ የሰሩትን ጅምር ቤት በብር 145‚000.00 በቀን 29/12/1999 ዓ/ም በተደረገ ውል ሽጠውልኝ ቤቱን አስረክበውኛል፡፡ ተጠሪ በስር በ1ኛ ተከሳሽ እግር ተተክቼ ከቀን 03/13/1999 ዓ/ም ጀምሮ በአባልነት ለማህበሩ የሚከፈሉ መዋጮዎችን እየከፈልኩ ቆይቻለው፡፡የግንባታ እቃዎችን በማቅረብ የጅምር ቤቱን ግንባታ በማጠናቀቅ ላይ እያለሁ የአሁን አመልካች ቤቱን ከስር 1ኛ ተከሳሽ ገዝቻለው በማለታቸው በፍ/ቤት ክርክር ተደርጎ በመ/ቁ 291299 ላይ በቀን 29/09/1999 ዓ/ም በተሰጠ ውሳኔ አመልካች ቤቱን በሕገ-ወጥ መንገድ ይዘዋል ተብሎ ቢወሰንም አመልካች እስካሁን ድረስ ቤቱን በህገ-ወጥ መንገድ ይዘውብኝ ይገኛሉ፡፡ ስለሆነም አመልካች ያስከተሉብኝን የንብረት ባለቤትነት ክርክር የስር 1ኛ ተከሳሽ ተከራክረው በማስመለስ የውል ግዴታቸውን እንዲወጡ እንዲወሰንልኝ ፡፡ የአሁን አመልካች በሕገ-ወጥ መንገድ የያዙትን ቤት ለቀው እንዲያስረክቡኝ እንዲወሰንልኝ፡፡እንዲሁም አመልካች ቤቱን በሕገ-ወጥ መንገድ በመያዛቸው ያጣሁትን ገቢ አሰልቼ መጠየቅ እንድችል መብት ተጠብቆ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡……….

Read more

እነ አቶ አድማስ አደመ ከ የባህደር ዙሪያ ወረዳ የገጠር መሬት አስተዳደር ፅ/ቤት የሰ/መ/ቁጥር 189495

Tuesday, April 6, 2021 19370

ክርክሩ የገጠር መሬት ይዞታን የሚመለከት ሲሆን ጉዳዩ በተጀመረበት የባህዳር ዙሪያ ወረዳ ፍ/ቤት ተጠሪ ከሳሽ አመልካቾች እንደየቅደም ተከተላቸው ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡

ተጠሪ ሐምሌ 25 ቀን 2011 ዓ.ም በተፃፈ ክስ በልጆሚ ቀበሌ አምላክ ጎጥ በምስራቅ መንገድ፣ በምእራብ የግጦሽ መሬት፣ በሰሜን የግጦሽ መሬት፣ በደቡብ ፍቅሬ ባየሕ የሚያዋስኑት ስፋቱ 2 ቃዳ መሬት የቀበሌው አስተዳዳሪ እየተቃወማቸው አመልካቾች በ2011 ዓ.ም ለ2012 ዓ.ም በማረስ ሩዝ የዘሩበት ስለሆነ መሬቱ እንደለበሰ ለቀው እንዲያስረክቡ ይወሰንልን በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡ …..

Read more

ወ-ሮ በድሪያ ዳውድ እና አቶ በርገና መሃመድ የሰ-መ-ቁ 184428

Monday, April 5, 2021 20175

የሰበር አቤቱታው የቀረበው አመልካች በቀን 03/02/2012 ዓ.ም በተጻፈ አቤቱታ የደ/ብ/ብ/ሕ/ክ/መ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ 13570 በቀን 28/12/2011 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ይታረምልኝ በማለት ስለጠየቁ ነው፡፡ ክርክሩ የጀመረው በስር የስልጤ ዞን በሳንኩራ ወረዳ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁን አመልካች ከሳሽ ተጠሪ ደግሞ ተከሰሽ ነበሩ፡፡ከመዝገቡ መረዳት እንደሚቻለው በወረዳ ፍ/ቤት የአሁን አመልካች በቀን 22/04/2011 ዓ.ም ባቀረቡት  አቤቱታ ተከሳሽ በወረዳው ልዩ ስሙ ሀያት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኝ ዘጠኝ ጥማድ መሬት ባለቤቴ ከሀይለ ስላሴ ግዜ ጀምሮ የያዘውና በደርግ ዘመን መሬት ለአራሽ ከተባለ በኋላም 1978 ዓ.ም አካባቢ ከእኔ ጋር ትዳር መስርተን በመሬቱ አብረን እየተጠቀምንበት ቤት ሰርተን ልጅ ወልደን በ1990 ዓ.ም ባለቤቴ ዘመድ ጥየቃ ብሎ ወደ ሀድያ ዞን ሲሄድ የተጠቀሰውን መሬት፣ አንድ በሬና እኔን ከነልጄ አደራ ብሎ ሔዶ ሊመለስ አልቻለም፤ ተከሳሽም በተጣለበት አደራ መሰረት መሬቱን ለግማሽ እያረሰ እየበላን ቆይቶ መጀመሪያ መሬቱ ላይ የነበረው ቤት የፈረሰ በመሆኑ መኪዬ ሰይድ የተባለ ግለሰብ ሌላ ቤት ሰርቶልኝ እየኖርኩ 2002 ዓ.ም አካባቢ በንፋስ በመውደቁ ድጋሚ ሊሰራልን ሲል ተከሳሽ በመከልከል ከራሱ ጋር እንድቀመጥ አድርጎ እስከ 2005 ዓ.ም ድረስ መሬቱን እያረሰ ቀለቤን እየሰጠኝ ከቆየ በኋላ በሬዬንም ሽጦ ለግልጥቅሙ በማዋልና የእኔን አቅመ ደካማነት መስማትና መናገር የማልችል ረዳት የሌለኝ መሆኔን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም መሬቱን በራሱ ስር በማድረግ ከኖርኩበት ቤት ከእነልጄ አፈናቅሎኝ በሽማግሌ ሲጠየቅ ከሳሽ ያላት ሁለት ጥማድ መሬት ብቻ ነው በማለት እሱንም ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ ስለሆነም አላግባብ የያዘውን መሬት እንዲለቅ፤ መሬቱ በስድስት አመት ውስጥ ቢከራይ ሊያወጣ የሚችለውን ዋጋ ብር 43,000.00 (አርባ ሶስት ሺህ)፣ ሽጦ ለግል ጥቅሙ ያዋለው የበሬ ዋጋ ብር 5000.00 (አምስት ሺህ)፣ ከቤት ንብረቴ አፈናቅሎኝ ለተለያየ እንግልት ለዳረገበት ብር 10,000.00 (አስር ሺህ) የሞራል ካሳ እና ለክስ ያወጣሁት ብር 5000.00 (አምስት ሺህ) በአጠቃላይ ድምር ብር 63,000.00 (ስልሳ ሶስት ሺህ) እንዲከፍለኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡……….

Read more

እነ አቶ ብርቄ ደስታ፣ወ-ሮ ላቀች ገብረወልድ እና ወ-ሮ ፈለቀች በልሄ የሰ-መ-ቁ 189274

Friday, April 2, 2021 19341

ይህ ጉዳይ የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ማማ ምድር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን ተጠሪዎች በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስ በ 012 ቀበሌ ልዩ ስሙ አመጃ ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ የሚገኘውንና መጠኑ አራት ጥማድ የሆነውን መሬታችንን አመልካች መብት ሳይኖራቸዉ በህገ-ወጥ መንገድ የይዞታ ማረጋገጫ አውጥተዉበት ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ ይዘዉ እየተጠቀሙበት ስለሆነ ለቀዉ እንዲያስረክቡን ይወሰንልን በማለት የጠየቀዉን ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ፡፡ አመልካች በበኩላቸዉ ክሱ በይርጋ ይታገዳል የሚለዉን የመጀመሪያ መቃወሚያ በማስቀደም ሌሎች የፍሬ ነገር ክርክሮችንም በማቅረብ ተከራክረዋል፡፡……….

Read more

ዘሀራ ሰዒድ እና የደቡብ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ መዝገቡ ሰ-መ-ቁ 193294

Friday, April 2, 2021 18163

ዘሀራ ሰዒድ እና የደቡብ ብሔሮች እና ብሔረሰቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ መዝገቡ ሰ-መ-ቁ 193294

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ.ም ጽፋ ባቀረበችው የሰበር አቤቱታ በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 31781 የካቲት 09 ቀን 2012 ዓ.ም በዋለው ችሎት በስሩ ያሉት ፍርድ ቤቶች የሰጡትን የጥፋተኛነት እና የቅጣት ውሳኔ በማጽናት የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረቧ ነው፡፡

ጉዳዩ ወንጀልን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የጂንካ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ነው፡፡ የአሁን ተጠሪ በአሁን አመልካች እና በስር 2ኛ ተከሳሸ ላይ በስር ፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ ይዘት በአጭሩ……..

Read more
FirstPrevious20212223242526272829NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions