Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • President Message
    • President
      • Current President
      • Former President
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • History and Traditions
    • Judges
      • Former Judges
    • Vision Mission and Mandate
    • Judicial Administration Council
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Tender
  • Judgement Execution Directorate
    • About Judgement Execution Directorate
    • Auction
  • Vacancy
  • Child Justice Project

እነ ሀድሌ ኢብራሂን እና እነ የጠይብ አብዲላሂ ሰ/መ/ቁ. 202114

Thursday, February 24, 2022 11071

ጉዳዩ እርሻ መሬትን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የጀመረውም በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፋፈን ዞን ጅግጅጋ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በስር ፍርድ ቤት በነበረው ክርክር አመልካቾች ከሳሽ፣ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ አመልካቾች በተጠሪዎች ላይ ባቀረቡተ ክስ በሰሀሊቲ ቀበሌ ኮጃርታ ሼህ ጣሂር ተብሎ ከሚጠራው ስፍራ በሰሜን ሀጂ መሀመድ እና የጎሳ ቦታ፣ በምዕራብ ሙሳ አውሌ፣ በደቡብ ተጠሪዎች፣ በምስራቅ የአመልካቾች መሬት የሚያዋስኑትን ስፋቱ 4 ጋሻ፣ ርዝመቱ ደግሞ 7.5 ጋሻ ጠቅላላ መጠኑ 30 ጋሻ የሆነ የእርሻ መሬት ያለአግባብ ይዘውብናል፤ እንዲለቁልን ብንጠይቃቸው ፍቃደኛ ስላልሆኑ ለቀው እንዲያስረክቡን ይወሰንልን በማለት ዳኝነት ጠይቀው ተከራክረዋል፡፡…………

Read more

ግርማ ለገሠ ተምትሜ እና የፐብሊክ ሰርቪስ ሠራተኞች ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት የሰበር መ/ቁ/202092

Wednesday, February 23, 2022 11957

ጉዳዩ የአሰሪና ሠራተኛ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ሲሆን የአሁኑ አመልካች ከሳሽ ፤የአሁኑ ተጠሪ (ተከሳሽ) በመሆን ተከራክረዋል፡፡አመልካች በተጠሪ ድርጅት ውስጥ ከጥር 13 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ በሾፈር ስራ መደብ ላይ እየሰራሁ እያለሁ ተጠሪ ድርጅት የጡረታ መውጫ ጊዜህ ከሐምሌ 1 ቀን 2011 ዓ.ም ጀምሮ መሆኑን በቁጥር ፐ/ሰ/ድ/386/2011 በቀን 18/11/2011 ዓ.ም ስራዬን እንዳቆም በደብዳቤ በገለጸልኝ መሰረት አስፈላጊውን ፎርማሊቲ አሟልቼ ስራዬን ከለቀቅኩኝ በኋላ ጡረታ ሚኒስቴር በመመላለስ የጡረታ አበል ለመቀበል እንዲችል በምጠይቅበት ጊዜ የጡረታ መውጫ ጊዜዬ ሐምሌ 1 ቀን 2011 ዓ.ም ሳይሆን ከሐምሌ 1 ቀን 2013 ዓ.ም መሆኑን ገልጸውልኝ ወደ ስራዬ እንዲመለስ ጡረታ ሚኒስቴር ለተጠሪ ሲጽፍ ተጠሪ ድርጅት ወደ ስራ እንዲመለስ እና ደመወዝ እንዲከፈለኝ ሲጠይቅ ፍቃደኛ ባለመሆኑ የጡረታ መውጫ ጊዜዬ እስኪደርስ ወደ መደበኛ ስራዬ እንዲመልሰኝ እና የተቋረጠብኝ ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም እንዲከፈለኝ እንዲወሰንልኝ የሚል ዳኝነት ያቀረበ ሲሆን ተጠሪ በበኩሉ የሰጠው መልስ የአመልካች ሥራ የተቋረጠው በተጠሪ ጥፋት ሳይሆን አመልካች ሲቀጠር የሕይወት ታርክ ቅጽ ሲሞላ የተወለደበት ቀን ራሱ የሞላው መሰረት ተድረጎ ስህተት የተፈጠረው አመልካች በሌላ ድርጅት ሲቀጠር የሞላው የትውልድ ዘመን እና በተጠሪ ድርጅት ሲቀጠር የሞላው የትውልድ ዘመን ሲጣራ የጡረታ እድሜ ያልደረሰ መሆኑን የጡረታ ሚኒስቴር ያረጋገጠ ሲሆን ተጠሪ ድርጅትም ከመስከረም 27 ቀን 2012 ዓ.ም ስራ እንዲጀምር ቢጠየቁም ውዝፍ ደመወዝ ካልተከፈለኝ በማለት ፍቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል፡፡………..

Read more

የደነባ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት እና አቶ ጥላሁን ይስማ ሰ/መ/ቁጥር 201201

Wednesday, February 23, 2022 11789

የቀረበው የሲያ/ዋዩ ወረዳ ፍርድ ቤት አመልካች ለአከራካሪው ቤትና ይዞታ በተጠሪ ስም የባለቤትነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰርቶ ሊሰጠው ይገባል በማለት የሰጠው ውሳኔ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች መፅናቱ  መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አመልካች ስላመለከተ ነው፡፡አመልካች በሲያ/ዋዩ ወረዳ ፍርድ ቤት ተከሳሽ የነበሩ ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ ነበሩ፡፡

ተጠሪ ህዳር 23 ቀን 2012 ዓ.ም ጽፈው በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስም አቶ ማናዜ መኮንን እና ወ/ሮ እትሞላሽ ደመቀ የነበራቸውን ጋብቻ በፍርድ ቤት አፍርሰው የጋራ ንብረታቸው የሆነውን በደነባ 01 ቀበሌ ሐ ዞን የሚገኘውን ቤትና ቦታቸውን ከተካፈሉ በኋላ ለአቶ ማናዜ የደረሳቸውን 187 ካሜ ቤትና ቦታ በ27/10/2006 ዓም በተደረገ ውል ገዝቼ አመልካችም ውል አዋውሎን፤ውሉን አፅድቆ በስሜ በማዞር የግንባታ ፈቃድ ሰጥቶኝ የነበረውን ቤት አፍርሼ ቤት የሰራሁበት ሲሆን ለይዞታዬ ካርታ እንዲሰጠኝ ስጠይቀው የቀበሌ ቤት አብሮ ስለተሸጠልህ አልሰጥህም ያለ ሲሆን ያሉትን አስተዳደራዊ መንገዶች ሁሉ ተጠቅሜ ጥያቄን ባቀርብም ምላሽ ያላገኘሁ በመሆኑ ለቤትና ለቦታው የባለቤትነት ማስረጃ እንዲሰጠኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡………

Read more

የፌዴራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ እና አበባየሁ ተዘራ የሰ.መ.ቁ 198703

Wednesday, February 23, 2022 12686

ጉዳዩ የወንጀል ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነው፡፡ አመልካች በተጠሪ ላይ በሥር ፍ/ቤት አቅርቦአቸው የነበሩት ክሶች ሁለት ሲሆኑ ይዘታቸውም፡-

1ኛ ክስ፡- ተጠሪ የወንጀል ሕጉን አንቀጽ 543(3) እና ደንብ ቁጥር 208/2003 አንቀጽ 26 ድንጋጌዎች በመተላለፍ የሌላውን ሰው ሕይወት፣ ጤንነት እና ደሕንነት የመጠበቅ የሙያ ግዴታ እያለባት ባለመወጣት በቀን 23/07/2010 ዓ.ም ከምሽቱ በግምት 1፡30 ሠዓት ሲሆን የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 2-57534 አ.አ የሆነ ተሸከርካሪ እያሽከረከረች ከስድስት ኪሎ ወደ መገናኛ አቅጣጫ ስትጓዝ የካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 07 ልዩ ቦታው ኮከበ ፅባሕ ትምህርት ቤት ፊት ለፊት ስትደርስ ለእግረኛ ቅድሚያ በመከልከል በእግረኛ ማቋረጫ መንገድ ላይ ስታቋጥ የነበረችውን ሟች አስምረት ንጉሴን በመኪናው የፊት ለፊት አካል ገጭታ በጭንቅላቷ ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ራሷን ስታ ወድያውኑ ሕይወቷ እንዲያልፍ በማድረግ በፈጸመችው በቸልተኝነት ሰውን መግደል ወንጀል ተከሳለች የሚል ነው፡፡……….

Read more

መሀመድ አባ ቡልጉ እና የጌምቤ ከተማ ማዘጋጃ ቤት የሰ.መ.ቁ 198400

Wednesday, February 23, 2022 12035

ጉዳዩ የይዞታ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በጅማ ዞን ጎማ ወረዳ ፍርድ ቤት ነው፡፡ በሥር ፍርድ ቤት በተደረገው ክርክር የአሁን አመልካች ከሳሽ፤ የአሁን ተጠሪ ተከሳሽ፤ በዚህ የሰበር ክርክር የሌለው የጌምቤ ከተማ መምሕራን ማህበር እነ አቶ ደሳለኝ አበበ / 14 ሰዎች ደግሞ ጣልቃ ገብ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ የአሁን አመልካች በሥር ፍ/ቤት ያቀረበው ክስ ይዘት በአጭሩ፡- አመልካች በሕጋዊ መንገድ የያዝኩት አንድ ፈጫሳ የቡና ችግኝ እና አንድ ፈጫሳ ባህር ዛፍ በ 2004 ዓ.ም ተክለው ጸድቆ የነበረ መሆኑን፤ ተጠሪ  ምንም ካሳ ሳይሰጣቸው ከአመልካች ወስዶ ለሰዎች ሲሰጥ የቀረውን አንድ ፈጫሳ በጌምቤ ከተማ ከሶ በር አካባቢ ተብሎ በሚጠራው አዋሳኙ በክሱ ላይ በተገለጸው ይዞታ ውስጥ በቀን 23/09/2011 ዓ.ም በመግባት አጠቃላይ ግምቱ ብር 3830 የሚያወጣ አራት ደጃፍ 3*4 የሆነ 10 ቅጠል ቆርቆሮ ቤት፤ መሪ እንጨት እና ማገር እንዲሁም ከንች ያፈረሰባቸው መሆኑን በመግለጽ አፍርሶ የወሰደውን የንብረት ግምት ብር 3830 / ሶስት ሺሕ ስምንት መቶ ሠላሳ ብር / እንዲከፍላቸው እና በይዞታቸው ላይ የፈጠረው ሁከት እንዲወገድ ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት መጠየቃቸውን የሚያሳይ ነው፡፡………..

Read more
Previous12345678910NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions