ጉዳዩ በአስተዳደር አካል የወጣ መመሪያ አግባብነት በፌደራል አስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2013 መሠረት እንዲከለስ የቀረበ አቤቱታ የሚመለከት ነዉ፡፡
ክርክሩ የተጀመረው የአሁኑ አመልካች ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረበዉ አቤቱታ ተጠሪ ነሐሴ ወር 2012 ዓ.ም ያወጣው የትምህርት አመራሮች ድልድል መመሪያ ህግን ባልተከተለ መልኩ ስለወጣ መመሪያው ተፈፃሚ እንዳይሆን እና እንዲከለስ የሚል ነዉ፡፡መልካም ንባብ………