Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • President Message
    • President
      • Current President
      • Former President
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • History and Traditions
    • Judges
      • Former Judges
    • Vision Mission and Mandate
    • Judicial Administration Council
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
    • NEWS
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Tender
  • Judgement Execution Directorate
    • About Judgement Execution Directorate
    • Auction
  • Vacancy
  • Child Justice Project

አቶ ሸምሱ አሊ እና ወ/ሮ ላይላ ኢታጎ የሰበር መዝገብ ቁጥር 216211

Friday, July 22, 2022 13788

ጉዳዩ በግራቀኙ መካከል የነበረው ጋብቻ በፍርድ ቤት የፍቺ ውሳኔ ከፈረሰ በኋላ በአመልካች እና ተጠሪ መካከል የተነሳውን የንብረት ክርክር በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሰጠውን ውሳኔ በመቃወም የቀረበውን ይግባኝ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አይቶ በሥር ፍርድ ቤት ተጣሪቶ ውሳኔ ሊያገኝ ይገባዋል ያለው ጭብጥ በመያዝ ወደ ሥር ፍርድ ቤት ከመለሰ በኋላ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የካቲት 22 ቀን 2013 ዓ/ም በዋለው ችሎት በጉዳዩ ላይ በሰጠው ውሳኔ ላይ የይግባኝ ቅሬታ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለማቅረብ የይግባኝ ቅሬታው የተዘጋጀ ቢሆንም ሲታመሙ የቆዩት  የአመልካች ጠበቃ ወላጅ እናት ሚያዝያ 20 ቀን 2013 ዓ/ም ሞተው ሚያዝያ 21 ቀን 2013 ዓ/ም የቀብር ሥርዓታቸው በመፈፀሙ ምክንያት በወቅቱ ይግባኝ ማቅረብ ስላልቻሉ ጊዜ ያለፈበትን ይግባኝ ማቅረብ እንዲችሉ እንድፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ……

Read more

ወ/ሮ ፍሬሕይወት ይልማ እና ፋና ቦሌ ሸማቾች ኃ/የተ/የሕብረት ሥራ ማሕበር የሰ/መ/ቁ. 216200

Friday, July 22, 2022 13017

የክርክሩን አመጣጥ ከሥር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው አመልካች በሥር ፍርድ ቤት ከሳሽ፤ ተጠሪ ተከሳሽ ነበሩ፡፡ አመልካች ሕዳር 30 ቀን 2013 ዓ/ም በተጻፈ ክስ በተጠሪ ማሕበር በምግብና መጠጥ ቁጥጥር ዋና ክፍል ኃላፊነት የሥራ መደብ ተቀጥሬ ስሰራ ከሕግ ውጭ የሥራ ውሌን በማቋረጡ በሕብረት ሥራ ማሕበራት ሕግና በተጠሪ መተዳደሪያ ደንብ መሠረት በሽምግልና ዳኞች እንዲታይ ዳኛ ለማስመረጥና ለማስመደብ ክስ አቅርቤ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመዝገብ ቁጥር 94768 ግንቦት 15 ቀን 2011 ዓ/ም በዋለው ችሎት ጉዳዩ በሽምግልና ዳኞች ሳይሆን በሥራ ክርክር ችሎት ነው የሚታይ በማለት ክሱን ውድቅ አድርጓል፡፡ ጉዳዩ በይግባኝ ሆነ በሰበር ችሎት ተቀባይነት ያላገኘ በመሆኑ የሥራ ክርክር ችሎት ክሴን ተቀብሎ ወደሥራ እንድመለስ እንዲወሰንልኝ፣ ተጠሪ ለመመለስ ፈቃደኛ ካልሆነ ካሣ፣ የሥራ ስንብት ክፍያ፣ የማስጠንቀቂያ ጊዜ ክፍያ፣ ክፍያ ለዘገየበት ቅጣት፣ የዓመት ዕረፍት ክፍያ፣ በ2006 ዓ/ም የሐምሌ ወር ደመወዝ፣ በ2006 ዓ/ም የቡና ገለባ ሽያጭ በሕብረት ሥምምነቱ መሠረት ሊከፈለኝ የሚገባ ብር 1,900.00 እንዲከፈለኝ፣ የሥራ ምስክር ወረቀት እንዲሰጠኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ አመልካች ባቀረበው የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አመልካች የሥራ መሪ በመሆናቸው ክሱ በሥራ ክርክር ችሎት ሊታይ አይገባም፣ ክሱ በይርጋ ቀሪ ነው በማለት ተከራክሯል፡፡መልካም ንባብ…..

Read more

ወ/ሮ ጽጌ ጅማ እና እነ አቶ ፀጋዬ ፈሲሳ የሰ.መ.ቁ.215435

Friday, July 22, 2022 14088

የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ የአሁን ተጠሪዎች (የሥር አመልካቾች) በሥር ፍ/ቤት ባቀረቡት ሟች አባታችን አቶ ፈሲሳ ሉቤ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 1 የቤት ቁ.161 ውስጥ እየኖሩ ባደረባቸዉ ሕመም ምክንያት በ13/10/1959 ዓ.ም ከዚህ ዓላም በሞት የተለዩ በመሆኑ፣ የሟች የውርስ ሀብት እንዲጣራልን በማለት ዳኝነት የጠየቁ ሲሆን፤ በፍ/ቤት የውርስ አጣሪዉ ተሹሞ የዉርስ ሀብቱ ተጣርቶ ዉሳኔ ከተሰጠ በኋላ የአሁን አመልካች (የሥር ጣልቃ ገብ) ለይግባኝ ሰሚዉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ይግባኝ አቅርባ ፍ/ቤቱም ባሳለፈዉ ዉሳኔ ጣልቃ ገብ ያቀረቡትን የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ላይ በቅድሚያ በማከራከርና ወደ ፍሬ ነገር የሚያስገባም ከሆነ አከራካሪዉ ቤትና ይዞታ ሟችና ጣልቃ ገብ በጋብቻ ውስጥ የተፈራ የጋራ ሀብት መሆን አለመሆኑ ግራ ቀኙን እንደገና እንዲያከራክርና የመሰለዉን ዉሳኔ እንዲሰጥበት ለፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት መልሶለታል፡፡መልካም ንባብ…..

Read more

እነ ወ/ሮ አርሴማ ኤልያ እና …….የሰ.መ.ቁ.215383

Friday, July 22, 2022 14745

የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ አመልካቾች በሥር ፍ/ቤት ባቀረቡት አቤቱታ 1ኛ አመልካች እና 2ኛ አመልካች ባልና ሚስት ሲሆኑ፣ 1ኛ አመልካች ከ2ኛ አመልካች የማትወለደውን ህጻን ልጃቸውን ህጋዊ ባለቤታቸው ለሆነው ለ2ኛ አመልካች በጉዲፈቻ ለመስጠት ያደረጉትን ስምምነት እንዲጸድቅላቸዉ ዳኝነት ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ…….

Read more

አቶ ኤልያስ ግደይ እና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ የሰ/መ/ቁጥር 215268

Friday, July 22, 2022 13748

ጉዳዩ በአስተዳደር አካል የወጣ መመሪያ አግባብነት በፌደራል አስተዳደር ስነ-ስርዓት አዋጅ ቁጥር 1183/2013 መሠረት እንዲከለስ የቀረበ አቤቱታ የሚመለከት ነዉ፡፡

ክርክሩ የተጀመረው የአሁኑ አመልካች ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባቀረበዉ አቤቱታ ተጠሪ ነሐሴ ወር 2012 ዓ.ም ያወጣው የትምህርት አመራሮች ድልድል መመሪያ ህግን ባልተከተለ መልኩ ስለወጣ መመሪያው ተፈፃሚ እንዳይሆን እና እንዲከለስ የሚል ነዉ፡፡መልካም ንባብ………

Read more
Previous12345678910NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions