Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • President Message
    • President
      • Current President
      • Former President
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • History and Traditions
    • Judges
      • Former Judges
    • Vision Mission and Mandate
    • Judicial Administration Council
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
    • NEWS
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Tender
  • Judgement Execution Directorate
    • About Judgement Execution Directorate
    • Auction
  • Vacancy
  • Child Justice Project

ሆሆተ ፋብሪካ ኃ/የተ/የግ/ማህበር እናወ/ሮ ዘውዲቱ በዳሶ የሰ/መ/ቁ 256580

Tuesday, June 17, 2025 5386

በከሳሽ የቀረበው ክስ ይዘት በአጭሩ ከአመልካች ፋብሪካ በሚወጣው መርዛማ ጭስ ምክንያት የግል ንብረቴ የሆነውን የሆላንድ ጥጃ ግምቱ ብር 10,000.00 (አስር ሺ) እና የሆላንድ የወተት ላም ብር 170,000.00 (አንድ መቶ ሰባ ሺህ) መስከረም 06 ቀን 2014 ዓ.ም ጥጃዋ ወዲያውኑ ስትሞት ላሚቷ መጋቢት 22 ቀን 2014 ዓ.ም ሞታለች፡፡ስለሆነም የሆላንድ ላሟ ከነጥጃዋ የዋጋ ግምት በድምሩ ብር 180,000.00 (አንድ መቶ ሰማኒያ ሺህ ) የሚያወጡ ሲሆን ላሟ ከመታመሟ በፊት በቀን 27 ሊትር ወተት የምትሰጥ ሲሆን የአንድ ሊትር ወተት ዋጋ ብር 40 የሚሸጥ በመሆኑ በቀን ብር 1080 (አንድ ሺህ ሰማኒያ) ሲሆን በወር ብር 32‚400 (ሰላሳ ሁለት ሺህ አራት መቶ ብር) ገቢ ሳገኝ የነበረ ሲሆን ላሟ ለሶስት ወር ከ 9 ቀናት ታማ ምርት በማቆም ስትታከም በነበረበት ያጣሁት ገቢ ብር 106,920.00 (አንድ መቶ ስድስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሃያ) ጨምሮ በአጠቃላይ ብር 286 920.00 (ሁለት መቶ ሰማኒያ ስድስት ሺ ዘጠኝ መቶ ሃያ  እንዲወሰንልኝ የሚል ነው፡፡ተጠሪም በሰጡት መልስ ፋብሪካው ሲቋቋም በአካባቢው ላይ ተጽዕኖ የማያደርስ ስለመሆኑ ተረጋግጦ ነው፣ የክርክር መነሻ የሆኑት ጥጃ የሞተችበት እና ላሚቷ የታመመችበት ጊዜ የአመልካች ፋብሪካ ስራ ያልጀመረ በመሆኑ ለላሞቹ ሞት ምክንያት የደረሰው ጉዳት ከፋብሪካው የወጣ ጭስ ሊሆን የማይችል በመሆኑ አመልካች ለተጠሪ ጥጃ እና ላም መሞት ኃላፊነት የለበትም፤ካሳ ለመክፈልም ሊገደድ አይችልም በሚል የቀረበው ክስ ውድቅ እንዲደረግ ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…

Read more

የኢትዮጵያ መድን ድርጅት እና አቶ አበራ ተፈሪ የሰ/መ/ቁጥር 254101

Tuesday, June 17, 2025 5366

ጉዳዩ የጉዳት ካሳን የሚመለከት ሲሆን ክሱ በጀመረበት የፌ/ከ/ፍ/ቤት አመልካች ተከሳሽ ተጠሪ ከሳሽ ነበር፡፡ ተጠሪ ያቀረቡት የክስ ይዘትም፡- የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-53974 ኢ.ት እንዲሁም ኮድ 3-1775 ኢ.ት ለሆነው ተሽከርካሪያቸው ከአመልካች አጠቃላይ የንግድ ተሸከርካሪ የመድን ዋስትና የገዙ መሆኑን፤ ይህ መድን የተገባለት ተሸከርካሪያቸው በስራ ላይ እያለ በምዕራብ ወለጋ ዞን መንዲ ተብሎ ከሚጠራ አካባቢ ህዳር 17 ቀን 2011 ዓ.ም ያልታወቁ ግለሰቦች አስገድደው እንዲቆም አድርገው ተሸከርካሪውን፤ጭኖት የነበረውን ቢራ እና የሽያጭ ደረሰኞች ይዘው መሰወራቸውን፤ ይህ ስርቆት መፈጸሙን የተጠሪ ወኪል እንዳወቁ ወዲያውኑ ለአመልካች ድርጅት አሶሳ ቅርንጫፍ ማሳወቃቸውን፤ ከበርካታ ክትትል በኋላ ነሀሴ 16 ቀን 2011 ዓ.ም ተሳቢው ምንም ጉዳት ሳይደርስበት የተገኘ መሆኑን እና ዋናው ተሸከርካሪ ግን ተቃጥሎ መገኘቱን፤ ነሀሴ 17 ቀን 2011 ዓ.ም ፖሊስ ባደረገው ሪፖርት ተሽከርካሪው እና ተሳቢው 2,400 ሳጥን ቢራ ጭኖ ከአ.አ ወደ አሶሳ በመጓዝ ላይ እንዳለ ህዳር 17 ቀን 2011 በሌቦች ተሰርቆ ዋናው ተሸከርካሪ በቃጠሎ ከጥቅም ውጭ ሆነ መገኘቱን መግለጹን፤አመልካች ካሳ እንዲከፍል ሲጠየቅ ደርጊቲ የተፈጸመው በሽፍቶች ነው፤ በኋላ  ላይ ደግሞ ድርጊቱ የተፈጸመው በጦርነት እንቅስቃሴ እና መሰል ሁኔታዎች ነው፤ እንዲሁም ስለድርጊቱ መከሰት አላሳወቃችሁኝም በማለት የካሳ ክፍያ ጥያቄአቸወን ውድቅ ማድረጉን ገልጸው ንብረቱ በእሳት ሙሉ በሙሉ የወደመ ስለሆነ በመድን ውሉ ለንብረቱ ከተሰጠው የዋስትና ጣሪያ ብር 2,000,000.00 ከተወሰነው የአደጋ መነሻ ውስጥ ከፍተኛውን 5 % ተቀናሽ በማድረግ 1,900,000.00 ከወጪና ኪሳራ ጋር አንዲከፍል ይወሰንልኝ ሲሉ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ…

Read more

ኤልያስ ዳሪ እና እነ ወ/ሮ ሰናይት አብርሃ (6) ሰዎች የሰ/መ/ቁ. 253783

Tuesday, June 17, 2025 5556

ጉዳዩ የሽያጭ ውል ይፈጸምልኝ ክስ ክርክርን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አመልካች ባቀረቡት ክስ 1ኛ ተጠሪ ሚስትና የወራሽ ወኪል ሆነው ከ3ኛ-6ኛ ያሉት ተጠሪዎች ጋር በጋራ በመሆን በድሮ ቂርቆስ ክ/ከተማ ወረዳ 3 የይዞታ መለያ ቁጥር AA000040301555 የሆነ በ348 ካ.ሜ ላይ ያለውን ቤትና ይዞታቸውን ጥቅምት 24 ቀን 2011 ዓ/ም በተደረገ የሽያጭ ውል በብር 2,900,000 ሸጠውልኝ በዚህ ውል መሰረት ለሻጮች በየድርሻቸው መጠን እንዲካፈሉት በቼክ ለሁሉም ግማሽ ክፍያው የተከፈላቸው ሲሆን በሽያጭ ውሉ መሰረት ውሉ በተደረገ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ የሽያጭ ውሉ ፎርማሊቲውን አሟልተው ውሉን በሰነዶች ምዝገባ ጽ/ቤት ቀርበው ሲያስመዘግቡና ቤትና ይዞታውን ከቤቱ አስረጂ ሰነድ ጋር ሲያስረክቡኝ ቀሪውን ገንዘብ ልከፍላቸው የተስማማን ሲሆን ተጠሪዎች በውሉ መሰረት እንዲፈጽሙ በተደጋጋሚ ብጠይቅም 1ኛ እና 2ኛ ተጠሪዎች ፍቃደኛ ሲሆኑ ከ3ኛ እስከ 6ኛ ያሉ ተጠሪዎች ግን ፍቃደኛ ባለመሆናቸው ተጠሪዎች በውሉ የተጠቀሰውን ቤት ከነይዞታው ቤቱን ከሚመለከቱ ሰነዶች ጭምር እንዲያስረክቡኝ እንዲወሰንልኝ፤ እንዲሁም የቤቱን ስመሀብት ከሻጮች ወደ ገዢ ለማስተላለፍ የሚያስፈልጉ ፎርማሊቲዎችን እንዲያሟሉ ይወሰንላቸው ዘንድ ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡መልካም ንባብ….  

Read more

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና አቶ መጣልኝ መላኩ የሰ.መ.ቁ.252953

Tuesday, June 17, 2025 5649

የጉዳዩ አመጣጥ ሲታይ ከሳሽ (የአሁን ተጠሪ) በሥር የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ባቀረበዉ የክስ አቤቱታ፡ ከሳሽ በ2005 ዓ.ም የ40/60 የመኖሪያ ቤት መርሃ ግብር ተመዝግቤ በአሁኑ ወቅቱ ባጠቃላይ 430000 ማለትም መቶ ፐርሰንት የቆጠብኩኝ በመሆኑ በዉሉና በመመሪያዉ መሰረት ቅድሚያ ዕጣ እንዲወጣልኝ መደረግ ሲገባዉ ከመመሪያዉ ዉጭ አርባ ፐርሰንት የቆጠቡ ሰዎች ተካተዉ እጣ እንዲወጣ በመደረጉ መብቴን አጣቧል፡፡ ከሳሽ ከ1ኛ ተከሳሽ ጋር ባደረግነዉ ዉል ቤቱን ሊያስገኝ የሚያስችል ዉል የተዋዋልንና ግዴታዬን የተወጣሁ ቢሆንም ሌሎች ተከሳሾችም በመመሪያ ቁጥር 21/2005 መሰረት የሚጠበቅባቸዉን አስተዳደራዊ ኃላፊነታቸዉን በመወጣት ቤቱን ሊያስረክቡኝ አልቻሉም፡፡ 1ኛ ተከሳሽ ከ3ኛ ተከሳሽ ጋር ባደረገዉ ሰነድ መሰረት ተገንብተዉ የተጠናቀቁትን ቤቶች ከቢሮዉ ተረክቦ በዉሉ መሰረት ቅድሚያ ማስረከብ ሲገባዉ ይህን ያላደረገ በመሆኑ፣ ሌሎች ተከሳሾችም ኃላፊነታቸዉን ያልተወጡ በመሆናቸዉ፣ በመመሪያዉና በዉሉ መሰረት ተገንብተዉ ከተጠናቀቁ ቤቶች ላይ ከአንዱ ሳይት እንዲወስድ ተከሳሾች በአንድነትና በነጠላ ኃላፊነት አለባቸዉ ተብሎ እንዲወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቋል፡፡መልካም ንባብ….

Read more

አቶ ኃይለ ጊዮርግስ ይልማ ወልደአብ እና እነ አቶ አዲስ እሸቱ (4) ሰዎች የሰ/መ/ቁ 252056

Tuesday, June 17, 2025 5577

ለዚህ የሰበር አቤቱታ ምክንያት የሆነዉ ክርክር የተጀመረዉ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ሲሆን በወረዳዉ ፍርድ ቤት 1ኛ ተጠሪ ከሳሽ የአመልካች አዉራሽ ሟች አቶ ይልማ ወልደአብና ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች ደግሞ ተከሳሽ በመሆን ተከራክረዋል፡፡ 1ኛ ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተራ ቁጥር ላይ በተጠቀሱት ተጠሪዎችና በአመልካች አባት በሟች አቶ ይልማ ወልደአብ ላይ ባቀረቡት ክስ በክሱ ላይ አዋሳኞቹ የተመለከተዉን 400 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈዉን  የመኖሪያ ቤት ከነሰርቪስ  ቤቶቹ ጭምር የካቲት 27 ቀን 2011 ዓ/ም በተፈረመ የሽያጭ ዉል ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (ከሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) በብር 200,000 (ሁለት መቶ ሺህ) ገዝተዉ ካርታ በስማቸዉ የተሰጣቸዉ ቢሆንም በይዞታዉ ላይ ካሉ ቤቶች መካከል አንዱን የአመልካች ወላጅ አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) ይዘዉ ለመልቀቅ ፈቃደኛ አለመሆናቸዉን ገልፀዉ ከ2ኛ እስከ 4ኛ ተጠሪዎች (የሥር 1ኛ እስከ 3ኛ ተከሳሾች) የሸጡላቸዉን ቤት ከአመልካች አባት (የሥር 4ኛ ተከሳሽ) አስለቅቀዉ እንዲያስረክቡና የአመልካች አባትም (የሥር 4ኛ ተከሳሽም) መብት ሳይኖራቸዉ የያዙትን የ1ኛ ተጠሪን (የሥር ከሳሽን) ቤት ለቀዉ እንዲወጡ እንዲወሰንላቸዉ ዳኝነት በመጠየቅ ክስ አቅርበዋል፡፡መልካም ንባብ….

Read more
Previous12345678910NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions