ጉዳዩ የጫት ሽያጭ ውልን መሰረት ያደረገ የእዳ ይከፈለኝ ክስን መሰረት ያደረገ ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የፋፈን ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተጠሪ ከሳሽ አመልካቾች እንደየቅደም ተከተላቸው ተከሳሾች በመሆን ተከራክረዋል፡፡
ተጠሪ ባቀረቡት ክስ ከአመልካቾች ጋር ባለን የጫት ንግድ ግንኙነት መነሻነት ጫቱን ቦንባስ አምጥቼ እያስረከብኳቸው ስንሰራ ቆይተናል፡፡ አመልካቾች ውሉን በራሳቸው ያቋረጡ ሲሆን ያለባቸውን የጫት ገንዘብ እዳ ብር 2,088,000 (ሁለት ሚሊዮን ሰማንያ ስምንት ሺ) እንዲከፍሉኝ ሽማግሌዎች ብልክባቸውም ፍቃደኛ ባለመሆናቸው እና እዳው በሰነድ የተመላከተ ስለሆነ በፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁጥር 284 መሰረት በተፋጠነ ስነ ስርዓት ገንዘቡን እንዲከፍሉ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡