Login
Federal Supreme Court of Ethiopia
Search
  • Home
  • About Us
    • President Message
    • President
      • Current President
      • Former President
    • Vice President
      • Current Vice President
      • Former Vice Presidents
    • History and Traditions
    • Judges
      • Former Judges
    • Vision Mission and Mandate
    • Judicial Administration Council
  • Court Services
    • Registry Services
      • Court Forms and Fees
    • Daily Court Trial Schedule
    • Case Tracker
    • Requesting Court Documents
      • Disposed Cases
    • Court Annexed Mediation
    • Interpretation Services
    • Legal Support
      • Child Justice Project Office
      • Public Defenders Office
  • Going to Court
    • Visiting the Court
      • What Can I see and Do?
    • Courtroom Etiquette
      • Courtroom Rules
    • Criminal: Information for the Accused Person
    • Civil Disputes: Information for Parties
    • Representing Yourself
    • Information for Witness
    • Information for Lawyers
    • FAQ
  • Digital Law Library
    • Annual Reports
    • State of the Judiciary
    • Monthly Judges Seminar
    • Federal Laws
    • Archives
    • Publications
      • Journal
      • Federal Cassation Decision Series
      • Newsletter
    • Judgments
      • Cassation Decisions
      • Supreme Court Decisions
  • News Media
    • Announcements
    • Interactives
      • Photos
      • Video
    • Services for Media
      • Press Releases
      • Press Conference
      • Media Advisories
      • Speeches
  • Contacts
    • Federal Supreme Court
    • Federal High Court
    • Federal First Instance Court
    • Contact and Feedback
  • Tender
  • Judgement Execution Directorate
    • About Judgement Execution Directorate
    • Auction
  • Vacancy
  • Child Justice Project

አቶ ተስፋዬ ኪዳኔ እና አቶ ወርቁ ዋበሎ የሰ/መ/ቁጥር 198071

Wednesday, February 23, 2022 11616

በዚህ መዝገብ ላይ የቀረበው ጉዳይ የከተማ ቦታን የሚመለከት ነው፡፡ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የሀዲያ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አመልካች አከራካሪውን ይዞታ በመልቀቅ ለተጠሪ ሊያስረክብ ይገባል በማለት የሰጠው ውሳኔ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች መፅናቱ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አመልካች ስላመለከቱ ነው፡፡አመልካች በሆሳዕና ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት ተከሳሽ የነበሩ ሲሆን ተጠሪ ከሳሽ ነበሩ፡፡

ተጠሪ የካቲት 19 ቀን 2011 ዓ.ም ጽፈው በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስም አዋሳኙ በክሱ ውስጥ የተጠቀሰውን በቢቾ ቀበሌ የሚገኘውን ይዞታ ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ በስጦታ አግኝቼ ቆርቆሮ ቤት ሰርቼ የምጠቀምበትን በ2008 ዓም በተደረገው ህገ ወጥ ይዞታን ስርአት የማስያዝ አሰራር ይዤ ካለሁበት 6 ሜትር መንገድ በመውሰዱ ወደ አመልካች ይዞታ ውስጥ ሲያስገባኝ አመልካችም ከኋላ ለኔ ለቅቆ ወደፊት እንዲሸጋሸግ ሲደረግ ለኔ በተሰጠኝ ይዞታ ላይ ቤት ገንብቶ ለመልቀቅ ፈቃደኛ ስላልሆነ በራሱ ወጪ አፍርሶ እንዲለቅልኝ ይወሰንልኝ በማለት ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡………….

Read more

አቶ ዮሀንስ ክፍሉ እና አቶ ሀሰን መሀመድ የሰ/መ/ቁጥር 197942

Wednesday, February 23, 2022 12151

ለዚህ የሰበር ክርክር መነሻ የሆነው ጉዳይ ተጠሪ ለአመልካች ለቅቆ ሊያስረክብ የሚገባው በተጠየቀው ዳኝነት አግባብ በምስራቅ አቅጣጫ 1 ሜትር × 14 ሜትር ሊሆን ይገባል በማለት የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ በክልሉ ሰበር ሰሚ ችሎት መፅናቱ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አመልካች ያቀረቡትን የሰበር አቤቱታ መነሻ ያደረገ ሲሆን ተጠሪ በጅማ ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት ከሳሽ የነበሩ ሲሆን አመልካች ተከሳሽ ነበሩ፡፡ተጠሪ በስር ፍርድ ቤት በአመልካች ላይ ባቀረቡት ክስም አዋሳኙ በክሱ ላይ የተመለከተውን በጅማ ከተማ ቦሳ ኪቶ ቀበሌ ውስጥ የሚገኝ 140 ካሜ መንግስት በሰጠኝ ቦታ ሰርቪስ ቤት ሰርቼበትና የይዞታ ማረጋገጫ አውጥቼበት የምጠቀምበትን በምስራቅ አቅጣጫ በኩል ወደ ይዞታዬ ርዝመቱ 1 ሜትር ቁመቱ 14 ሜትር በመግባት ግንባታ አከናውኖበት የያዘ ስለሆነ ግንባታውን አንስቶ ይዞታዬን እንዲለቅልኝ ይወሰንልኝ በማለት አመልክተዋል፡፡………….

Read more

የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤሕግ እና መልካሙ ዳታ ደሴ የሰ.መ.ቁ 197432

Wednesday, February 23, 2022 12013

የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች ጥቅምት 20 ቀን 2013 ዓ.ም ጽፎ ባቀረበው የሰበር አቤቱታ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በመ.ቁ 192545 ሐምሌ 27 በቀን 2012 ዓ.ም የሰጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስሕተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አቤቱታ በማቅረባቸው ነው፡፡ጉዳዩ ወንጀልን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ የተጀመረው በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ነው……………..

Read more

አቶ ኃይለጊዮርጊስ ይልማ እና አቶ አዲስ እሸቱ የሰ/መ/ቁጥር 197009

Wednesday, February 23, 2022 11135

ይህ የሰበር አቤቱታ ሊቀርብ የቻለው አመልካች እና በስር ፍርድ ቤት ከ1ኛ እስከ 3ኛ የተመለከቱት ተከሳሾች አከራካሪውን ቤት ለተጠሪ ሊያስረክቡ ይገባል በማለት የስር የጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ በየደረጃው ባሉ ፍርድ ቤቶች መፅናቱ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በማለት አመልካች ያቀረቡትን የሰበር አቤቱታ መነሻ በማድረግ ሲሆን ተጠሪ በጣርማ በር ወረዳ ፍርድ ቤት ከሳሽ የነበሩ ሲሆን አመልካች 1ኛተከሳሽ ነበሩ፡፡

ተጠሪ በስር ፍርድ ቤት በአመልካች እና በስር ፍርድ ቤት ከ1ኛ እስከ 3ኛ በተመለከቱት ተከሳሾች ላይ ባቀረቡት ክስም አዋሳኙ በክሱ ላይ የተመለከተውን 400 ካሜ ላይ ያረፈ መኖሪያ ቤት ከነሰርቪሱ የካቲት 27 ቀን 2011 ዓም በተደረገ የሽያጭ ውል ከ1ኛ እስከ 3ኛ ከተመለከቱት ተከሳሾች በብር 200,000.00 ገዝቼ ካርታ በስሜ የተሰጠኝ ቢሆንም ቤቱን ከአመልካች ነፃ በማድረግ ያላስረከቡኝ በመሆኑ ፤አመልካችም በአደራ ይዤ የምጠቀመው ነው በማለት ምንም መብት ሳይኖረው ለማስረከብ ፍቃደኛ ስላልሆነ ከ1ኛ እስከ 3ኛ የተመለከቱት ተከሳሾች ቤትና ይዞታውን ከ3ኛ ወገን ነፃ አድርገው እንዲያስረክቡኝ አመልካችም የፈጠረውን ሁከት አቁሞ ቤትና ቦታውን እንዲያስረክበኝ ይወሰንልኝ በማለት አመልክተዋል፡፡……..

Read more

አቶ ሀብታሙ ዝናቡ እና አቶ ታሪኩ አየለ የሰ/መ/ቁ 196871

Wednesday, February 23, 2022 15770

በዚህ መዝገብ ላይ የቀረበው ጉዳይ የከተማ ይዞታ ክርክርን የሚመለከት ነው፡፡ የሰበር አቤቱታው የቀረበው የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመ/ቁ/333779 ላይ ጥቅምት 03/2013 ዓ.ም በዋለው ችሎት የስር ፍርድ ቤቶችን ውሳኔን በማፅናት የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው በማለት ለማስለወጥ ነው፡፡

ክርክሩ የተጀመረው የአሁን ተጠሪ ሐምሌ 05/2011 ዓ.ም ፅፈው በአሁን አመልካች ላይ በጅማ ወረዳ ፍ/ቤት ባቀረቡት ክስ ነው፡፡ ፍሬ ቃሉም ቦታ እና አዋሳኙ በክሱ ዝርዝር ውስጥ የተጠቀሰውን 200 ካሬ ሜትር የከተማ ይዞታ ነሐሴ 06/2011 ዓ.ም ተሰጥቷቸው አስፈላጊውን ክፍያ ፈፅመው እና የግንባታ ፈቃድ አውጥተው በቦታው ላይ ግንባታ ለማከናወን ሲሄዱ ባላወቁት መንገድ የአሁን አመልካች ትንሽ ሰርቪስ ቤት ሰርተዉበት የያዙባቸው መሆኑን በመግለፅ በፍርድ ኃይል ተገደው በቦታው ላይ የሰሩትን ቤት አፍርሰው እንዲለቁላቸው ዳኝነት የሚጠይቅ ነው፡፡……………

Read more
Previous12345678910NextLast

Categories

  • 2011 Expand/Collapse
  • 2012 Expand/Collapse
  • 2013 Expand/Collapse
    Contacts
  • TEL : +251-11-1-55-34-00 /
  •          +251-11-1-11-04-32
  • Fax : +251 111-550278 /
  •          +251 111-565583
  • Email : fscpublicrelation@gmail.com
  • Address: 6 Killo , Addis Ababa, Ethiopia
Quick Links
  • About Us
  • E-Filing 
  • Calendar
  • Press Release
  • Case Tracker
  • FAQ
    Connect With Us
  • Privacy Policy
  • |
  • Site Map
Copyright © The Federal Supreme Court of Ethiopia- All rights reserved
Powered By Bsquare IT Solutions