17
ይህ ጉዳይ የዉርስ ሀብት ጥያቄን የሚመለከት ሲሆን ተጠሪዎች በስር በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ባቀረቡት ክስ የአመልካቾች አባት ሟች አቶ ዘለቀ ሀሰን በህይወት እያሉ የካቲት 13 ቀን 1990 ዓ.ም በተደረገ የመንደር ሽያጭ ዉል ለተጠሪዎች አባት ሟች ተገኝ ድረስ በሽያጭ ያስተላለፉት በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 10 አዋሳኞቹ በክሱ በተጠቀሰዉ ቦታ በ500 ካ/ሜትር ላይ ያረፈ ቤት እና ይዞታ የተጠሪዎች በመሆኑ ለአመልካቾች በዉርስ የሚተላለፍ ሀብት እንዳልሆነ በዉርስ አጣሪ ተጣርቶ በፍርድ ቤት ተወስኖ ያደረ መሆኑን በመጥቀስ ቤቱን አመልካቾች ያስረክቧቸዉ ዘንድ የጠየቁትን ዳኝነት መነሻ ያደረገ ነዉ፡፡ አመልካቾች ለክሱ በሰጡት መልስ የተሻረ ዉሳኔን መሰረት በማድረግ የቀረበ ነዉ፤ እንዲሁም ከሦስት ዓመት በኋላ የቀረበ የዉርስ ጥያቄ በመሆኑ ክሱ በይርጋ ይታገዳል የሚል የመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ በማስቀደም በፍሬ ነገር ረገድ በሰጡት መልስ ተጠሪዎች ለክሳቸዉ መሠረት ያደረጉት የሽያጭ ዉል በህግ አግባብ የተደረገ ባለመሆኑ እንደማያስገድዳቸዉ እና የዉርስ አጣሪ ሪፖርትም ሊስተባበል የሚችል ከመሆኑም በላይ የዉርስ አጣሪ ሪፖርት የጸደቀበት መ/ቁጥር 96840 በ/ቁጥር ይግባኝ ቀርቦበት በከፍተኛ ፍርድ ቤት በመ/ቁጥር 250878 የተሻረ መሆኑን ጠቅሰዉ የቀረበባቸዉ ክስ ዉድቅ እንዲደረግ ተከራክረዋል፡፡ጥሩንባብ…
21
የሰበር አቤቱታው ሊቀርብ የቻለው አመልካች ሰኔ 10 ቀን 2014 ዓ.ም ጽፈው ባቀረቡት የሰበር አቤቱታ የአ/ብ/ክ/መ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 112524 በቀን 18/09/2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት የአ/ብ/ክ/መ ሲቪል ሰርቪስ አስተዳደር ፍ/ቤት በመ/ቁ 11067/13 በቀን 09/01/2014ዓ.ም በዋለው ችሎት የወሰነውን ውሳኔ እና የአ/ብ/ክ/መ ጠቅላይ ፍ/ቤት መደበኛ ችሎት በመ.ቁ 58115 በቀን 07/07/2014 ዓ.ም በዋለው ችሎት የሰጠውን ትእዛዝ በመሻር የሰጠው ውሳኔ መሰረታዊ የህግ አተረጓጎም ስህተት የተፈጸመበት ነው በማለታቸው ሲሆን በስር የአስተዳደር ፍ/ቤት አመልካች ይግባኝ ባይ ሆነው ተጠሪ ደግሞ መልስ ሰጪ በመሆን ክርክር አድርገዋል፡፡ መልካም ንባብ…
15
በዚህ መዝገብ የተያዘው ክርክር እስራኤል ሀገር በሚኖሩት የአሁን አመልካች እና በአማራ ክልል ደልጊ ከተማ ነዋሪ ናቸው በተባሉት የአሁን ተጠሪ መካከል አስቀድሞ ተደርጎ ነበር የተባለ ጋብቻ እንዲፈርስ በዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረበ አቤቱታን የሚመለከት ነው፡፡ ክርክሩ በማዕከላው ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍ/ቤት የተጀመረ ሲሆን የአሁን አመልካች ተከሳሽ፤ የአሁን ተጠሪ ደግሞ ከሳሽ ነበሩ፡፡
ተጠሪ ባቀረቡ አቤቱታ ከአመልካች ጋር በነሀሴ 7 ቀን 2008 ዓ/ም በሀገር ባሕል መሰረት ጋብቻቸውን እንደፈጸሙ እንዲሁም ይኸው ጋብቻ በክብር መዝገብ ሹም ፊት እንደተመዘገ በመግለጽ በአሁኑ ወቅት በተጠሪ እና በአመልካች መካካከል አለመግባባት በመፈጠሩ ጋብቻው በፍ/ቤት ውሳኔ እንዲፈርስና የጋራ ሀብት እንዲካፈሉ እንዲወሰን ጠይቀዋል፡፡ ጥሩ ንባብ…
13
ለዚህ ሰበር ክርክር መነሻ የሆነው የሥራ ክርክር ሲሆን የተጀመረው በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ወሳኝ ቦርድ ነው፡፡ በወሳኝ ቦርዱ አመልካች ከሳሽ ሲሆን የአሁን ተጠሪ ደግሞ ተከሳሽ ነበሩ፡፡ የሰበር አቤቱታዉ የቀረበዉ ፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት በመ/ቁ 277127 ግንቦት 16 ቀን 2014 ዓ.ም በዋለዉ ችሎት የቡርዱን ዉሳኔ በመሻር የሰጠዉ ዉሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት የተፈጸመበት በመሆኑ ሊታረም ይገባል በሚል ነዉ፡፡
አመልካች ነሐሴ 06 ቀን 2013 ዓ.ም በተጻፈ አቤቱታ ያቀረቡት ክስ ይዘት፡- የደረጃ እድገት ለመስጠት ተጠሪ ባወጣዉ የዉድድር ማስታወቂያ በሥራ መደቡ ላይ ለ3 ዓመት ያህል ማገልገሉን፤ የዉድድሩን መስፈርት በማሟላት መመዝገባቸዉን፤ በመወዳደሪያ መስፈርቱ መሠረት ቀጥታ የሥራ ልምድ ያለዉ ሠራተኛ 20% 2/3ኛ ያገኛል፡፡ አመልካች በዉድድሩ አሸናፊ ከተደረገዉ ግለሰብ የተሻለ የትምህርት ዝግጅትና ነጥብ ሊሰጠዉ እየተገባ ያልተሰጠዉ መሆኑን፤ ተቀራራቢ የሥራ ልምድ እያላቸዉ የተለያዬ ዉጤት በመስጠት ዉጤቱ ዝቅተኛ እንዲሆን መደረጉን፤ የሥራ አፈጻጸም ምዘና ዉጤቱም ሆን ተብሎ ዝቅተኛ እንዲሆን ተደርጎ የደረጃ እድገቱ ለሌላ ግለሰብ እንዲሰጥ መደረጉ ተገቢ ባለመሆኑ የደረጃ እድገቱ ለአመልካች እንዲሰጥ የሚጠይቅ ነዉ፡፡ጥሩ ንባብ…
17
አመልካች መኖሪያ ቤት ውስጥ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ መኖሩ ለፖሊስ በደረሰው ጥቆማ ግንቦት 3 ቀን 2013 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 2፤30 ፍተሻ ሲደረግ በሕጋዎ መንገድ ከያዘው 30(ሰላሳ) ፍሬ የክላሽ ጥይት ውጪ 29(ሃያዘጠኝ) የክላሽ ጥይት እንዲሁም በሕጋዊ መንገድ እንዲይዝ ከተፈቀደለት 8(ስምንት) የሽጉጥ ጥይት ውጪ በቁጥር 25 (ሃያ አምስት) ጥይት በድምሩ 54(ሃማሣ አራት) የጥይት ፍሬዎች በቤቱ አስቀምጦ በመገኘቱ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የጦር መሣሪያ አስተዳደር እና ቁጥጥር አዋጅ ቁጥር 1177/2012 ቁጥር 22(3) የተደነገገውን በመተላለፍ ሕገ-ወጥ የጦር መሣሪያን አስቀመጧል በማለት ከሷል፡፡ ጥሩ ንባብ…