25
ጉዳዩ ለክርክሩ ምክንያት የሆነው ንብረት የውርስ ሀብት መሆን ያለመሆኑን የሚመለከት ሲሆን ክርክሩ በተጀመረበት በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአሁን አመልካቾች ተከሳሾች፤ ከ1ኛ-4ኛ ያሉት ተጠሪዎች የመቃወም አመልካቾች ከ5ኛ አስከ 7ኛ ያሉት ተጠሪዎች ደግሞ ከሳሾች በመሆን ተከራክረዋል፡፡
ከ1ኛ-4ኛ ያሉት ተጠሪዎች በመጋቢት 22 ቀን 2009 ዓ.ም የተጻፈ መቃወሚያ ያቀረቡት አመልካቾች እና ከ5ኛ-7ኛ ያሉት ተጠሪዎች በየካቲት 09 ቀን 2009 ዓ.ም የእርቅ ስምምነት አድርገው በፍርድ ቤት እንዲመዘገብ ማድረጋቸው በውርስ ሀብት ላይ ያለንን መብት ይነካል በሚል ነው፡፡ ጥሩ ንባብ…
20
የሰበር አቤቱታው የቀረበው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሰጠው ውሳኔ ላይ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በማለት ነው፡፡ በሥር ፍርድ ቤት አመልካች ከሳሽ፤ ተጠሪዎች ተከሣሾች በመሆን ተከራክረዋል፡፡ አመልካች ጥር 12 ቀን 2012 ዓ/ም በተፃፈ ክስ አመልካች ድርጅት በሀገራችን ውስጥ ለረጅም ዓመታት በአስቸኳይ ጊዜ እርዳትና ልማት ሥራ ሲያገለግል የቆየ ነባር ድርጅት ነው፡፡ጥሩ ንባብ...
25
ጉዳዩ የባልና ሚስት ጋብቻ ፍቺን ተከትሎ የቀረበን የጋራ ንብረት ክፍፍል ክርክርን የሚመለከት ሲሆን የአሁን አመልካች በግራቀኙ መካከል በ13/08/2001 ዓ.ም የተደረገው ጋብቻ በ27/11/2013 ዓ.ም በተሰጠ ውሳኔ መፍረሱን ተከትሎ የተለያዩ አልባሳት፣ የንብረት ክፍፍል እንዲደረግ የጠየቁ ሲሆን ክፍፍል ከተጠየቀባቸው ንብረቶች መካከል በኦሮሚያ ክልል ሱሉልታ ከተማ ቀበሌ 01 የቤት ቁጥር አዲስ ቄራ አካባቢ 3 ከፍል ጭቃ እና 1 ክፍል ቆርቆሮ በቆርቆሮ የተሰራ የቦታው ስፋት 560 ካ.ሜ የሆነ በብር 2,500 የሚከራይ ቤት፤ በተጠሪ ስም የተመዘገበ የኮንደሚኒየም ቤት፤ የተለያዩ የቤት ቁሳቁስ የጋራ ንብረት በመሆናቸው የጋራ ነው ተብሎ እንዲካፈሉ እንዲወሰንላቸው ዳኝነት ጠይቀዋል፡፡ጥሩ ንባብ…
20
የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው ተጠሪ በአመልካች እና ክሱ በተቋረጠላት አልማዝ ደረጀ ላይ ያቀረበው ክስ የወ/ሕ/ቁ. 32(1)(ሀ)፣ 27(1) እና 539(1)(ሀ) የተመለከተውን በመተላለፍ በወምበራ ወረዳ ጎቸር ቀበሌ የካቲት 09 ቀን 2012 ዓ/ም ሕዳር 15 ቀን 2012 ዓ/ም ከቀኑ 12፡00 ሰዓት የግል ተበዳይ ገሰሰ አያናን ሆነ ለመግደል በማሰብ ከገበያ ወደቤቱ እየሄደ ባለበት አመልካች ድንጋይ ከመሬት አንስቶ ሁለት ጊዜ ወርውሮ በመሳት ይዞት በነበረው አንካሴ አንድ ጊዜ ወርውሮ ከሳተው በኋላ እንደገና ድንጋይ ወርውሮ አራት ጊዜ ጥርሱ ላይ በመምታት ጥርሶችን ያወለቀ ሲሆን የግል ተበዳይ ሲወድቅ ጨካኝና ነውረኝነት በሚያሳይ መልኩ በዱላ ጭንቅላቱን፣ አፉና ጆሮውን ከመታው በኋላ እንደገና በያዘው አንካሴ በብረቱ በኩል የግራ አይን ቅንድቡን፣ ከንፈሩ ላይ በመውጋትና መላ ሰውነቱን በመደብበድ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱበት ስለሆነ በከባድ ሰው ግድያ ሙከራ ወንጀል ፈጽሟል በማለት ነው፡፡ መልካም ንባብ…
25
የሰበር አቤቱታው የቀረበው የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ችሎት የሠጠው ውሳኔ መሠረታዊ የሕግ ስህተት ተፈጽሞበታል በሚል ነው፡፡ የክርክሩን አመጣጥ ከስር ፍርድ ቤት የመዝገብ ግልባጭ እንደተረዳነው አመልካች በስር ፍርድ ቤት ከሳሽ፤ ተጠሪ ተከሳሽ ሆነው ተከራክረዋል፡፡ ለዚህ ሰበር ክርክር መነሻ የሆነው አመልካች በ16/06/2013 ዓ/ም አሻሽለው ባቀረቡት ክስ ተጠሪ በጎሎልቻ ወረዳ በሌሊሳ ነጋ ቀበሌ የሚገኘውን ስፋቱ 8 ሔክታር የሆነውን ይዞታ ውስጥ 5.045 ሔክታር የይዞታ ማረጋገጫ ወረቀት በላዩ በስሜ ተሰጥቶኛል፣ ተጠሪ ከሐምሌ ወር 2011 ዓ.ም ጀምሮ ያለፈቃዴ ከይዞታዬ ላይ አፈርና አሸዋ እያወጡ እየሸጡ ስለሆነ በላዩ አምርቼ እንዳልጠቀም አድርገውኛል በሚል ነው፡፡ ጥሩ ንባብ…